ክህሎት መር ስልጠና በመተግበር በሀገሪቱ ያለውን ፀጋ ተጠቅሞ በትጋት ሊሠራ እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 05/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለወጣቱ የሚሰጠው ክህሎት መር ስልጠና በሀገሪቱ ያለውን ፀጋ ተጠቅሞ በትጋት ሊሠራ እንደሚገባ የጌዴኦ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ ገለፀ።
መምሪያው የሥራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 1ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የቀጣይ 90 ቀናት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ አካሂዷል።
ወጣቶችን በየሥራ ዘርፉ ለይቶ የክህሎት ስልጠና ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር ተቀናጅተው መስጠት እንዲጀምሩ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠር የገደብ ከተማና የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስምምነት ተሰማ እና ተካልኝ በቀለ ተናግረዋል፡፡
የዞኑ ሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደለ ጥላሁን በ2018 መጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ላይ ውስንነቶች መካከል የመስሪያ ቦታ ከማመቻቸት ፣ በብድር ስርጭትና አመላለስ ዙሪያ ላይ መምከራቸውን አስታውሰዋል፡፡
ወጣቱ የሚሰጠውን ክህሎት መር ስልጠና በመተግበር በሀገሪቱ ያለውን ፀጋ ተጠቅሞ በትጋት ሊሠራ ይገባል ያሉት አቶ ታደለ አሁን ያለንበት ወቅት ቡና የሚሰበሰብት በመሆኑ ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር እንደሚፈጸም ጠቁመው ቁጠባ በማሰባሰብ ላይ ትኩረት እንዲደረግ በውይይቱ አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
አዲሱን የገቢ ግብር አዋጅ መሰረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ
በፍትህና የህግ መዋቅሮች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ አደረጃጀቶችን ከመፍጠር አንጻር የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተገለጸ
ታራሚዎች በስነ ምግባርና በሙያ ታንፀው ብቁ ዜጎች እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የሳውላ ማረሚያ ተቋም አስታወቀ