በከተማው ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት በቂ ባለመሆኑ መቸገራቸውን በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ውሃ አገልግሎት በበኩሉ በከተማው ያለውን የውሃ ችግር ለመፍታት እየሠራ መሆኑን ገልጿል።
ወ/ሮ አበበች ሽብሩ፣ አቶ ታደለ አበበ እና ሌሎችም የከተማዋ ነዋሪዎች፥ ይርጋጨፌ ውሃማ አካባቢ እንደሆነች የሚታወቅ ቢሆንም በተለይም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለማግኘት መቸገራቸውን ነው የሚገልጹት።
በከተማው ላይ የውሃ አቅርቦት በቂ ካለመሆኑ የተነሳ ንፁህ ያልሆነ የምንጭ ውሃ ለመጠቀም እንደሚገደዱና ለተለያዩ የውሃ ወለድ በሽታዎች እንደሚዳርጋቸውም ተናግረዋል።
የሚመለከታቸው አካላት ህብረተሰቡን በማስተባበር ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚዎች እንዲያደርጓቸው በመሥራት ችግሩን እንዲፈቱ ጠይቀዋል።
የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ውሃ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ታሪኩ፤ በከተማዋ ያለው የውሃ ሽፋን ዝቅተኛ ወይም 15 በመቶ ብቻ እንደሆነ ጠቁመው ህብረተሰቡ የሚያነሳው ቅሬታ ትክክል እንደሆነ ገልጸዋል።
ከጊዜ ወደጊዜ የህዝብ ቁጥር መጨመር፣ ከአገልግሎት ብዛት የተነሳ የውሃ ፓምፖች ብልሽት፣ የመብራት መቆራረጥና ኃይል ማነስ በዋናነት በከተማዋ ላለው የውሃ ችግር በምክንያትነት አንስተዋል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር እየሠሩ እንዳሉ በመግለፅ ህብረተሰቡም የድርሻውን መወጣትና ማገዝ አለበት ብለዋል።
ዘጋቢ: ለምለም ኦርሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ታራሚዎች በስነ ምግባርና በሙያ ታንፀው ብቁ ዜጎች እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የሳውላ ማረሚያ ተቋም አስታወቀ
20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ የተዘጋጀ የአሰልጣኞች ስልጠና መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው
የደቡብ ኦሞ ዞን ሽግግር ምክር ቤት የአስፈጻሚ ተቋማት አፈጻጸም ምልከታው በዳሰነች ወረዳ ቀጥሏል