አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት በተቀላጠፈ መልኩ መስጠት እንዳለባቸው ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት በተቀላጠፈ መልኩ መስጠት እንዳለባቸው የሀዲያ ዞን ፍትህ መምሪያ አስገነዘበ።
አግባብነት በሌለው ሁኔታ ተገልጋይን ማጉላላት ለተጠያቂነት የሚዳርግ መሆኑ አመላክቷል።
በሀዲያ ዞን ፍትሕ መምሪያ የሕግ ጥናት ማርቀቅ እና ማስረጽ ስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ወንድሙ ስነሞ እንደገለፁት÷ መንግስት ሕብረተሰቡ የልማትም ሆነ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን ባጠረ ጊዜና ጥራት ባለ መልኩ እንዲያስፈጽም የስራ ዘርፎችን በመቅረጽ ማመቻቸቱን ጠቁመው÷ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ አገልገሎት ሰጭ ተቋማት የሚሰሩ ባለሙያዎች የተሰጣቸውን የስራ ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው አሳማኝ ያልሆኑ ምክንያቶችን በመፍጠር ባለጉዳዮችን ሲያጉላሉ ይስተዋላል ብለዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ባለጉዳይን በተገቢው መንገድ ያለማስተናገድ ለህጋዊ ቅጣት እንደሚዳርግ አመላክተዋል።
በሙስና የተገኘ ሀብት እንደሚወረስ አዋጁ ይደነግጋል ያሉት አቶ ወንድሙ በማንኛውም አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ላይ የሚሰሩ ሀላፊዎችም ሆኑ ሠራተኞች የተሰጣቸውን የስራ ሀላፊነት ከሙስናና ብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
ሕብረተሰቡም ያለአግባብ የሚያጉላሉ አመራሮችንም ሆነ ሠራተኞችን አጋልጦ በመስጠት በሕግ አግባብ ተግባራት እንዲፈፀሙ በሚደረጉ ጥረቶች የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።
ዘጋቢ: ጌታቸው መጮሮ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ