ሴቶች የቁጠባን ባህል በማዳበር የኢኮኖሚ አቅማቸውን ለማሳደግ በትጋት ሊሠሩ እንደሚገባ ተገለጸ
”ትጋት ለላቀ ስኬት!” በሚል መሪ ቃል የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዞን ማዕከል ፐብሊክ ሰርቫንት የሶስቱም ዘርፍ ህብረት የ2018 ዓ/ም 1ኛ ሩብ ዓመት የአባላት ኮንፈረንስ ተካሂዷል።
በጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በልማት ስራዎች የሴቶችን ንቁ ተሳትፎ በማሳደግ በሩብ ዓመት አፈፃፀም የተሻለ ውጤት ማስመዝገባቸውን በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የዞኑ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊና የሴቶች ክንፍ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሊዲያ ከበደ ናቸው፡፡
እንደ አካባቢያችን አሁን ያለንበት ወቅት ምርት የሚሰበሰብበትና ገንዘብ የሚገኝበት በመሆኑ ሴቶች የቁጠባን ባህል በማዳበር የኢኮኖሚ አቅማቸውን ለማሳደግ በትጋት እንዲሠሩ ወ/ሮ ሊዲያ ጠቁመው÷ በአፈፃፀሙ በተሻለ የተመዘገቡትን ይበልጥ ማጠናከርና በውስንነት የተስተዋሉትን ማረም እንደሚገባ ኃላፊዋ አመላክተዋል፡፡
የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ ወ/ሮ የሺወርቅ ጥላሁን እንደገለፁት በሩብ ዓመቱ አፈፃፀም የሴቶች አባላት ኮንፈረንስ በየመዋቅሩ በተደራጀ መልኩ መካሄዱን ገልጸው÷ በክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሴቶች አደረጃጀት ለችግር ተጋላጭ ለሆኑት ወገኖች ደርሰው እንባቸውን በማበስ የበኩላቸውን መወጣታቸውን አስታውቀዋል፡፡
በሩብ ዓመቱ አፈፃፀም በሴቶች መሪነት በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቀሴዎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸን የጠቀሱት ወ/ሮ የሺወርቅ በሌማት ትሩፋት ሥራዎች ፣ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናና የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ በንቃት መሳተፋቸውን ገልጸዋል።
ዘጋቢ: ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ሴቶች የቁጠባን ባህል በማዳበር የኢኮኖሚ አቅማቸውን ለማሳደግ በትጋት ሊሠሩ እንደሚገባ ተገለጸ

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ