የሳውላ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽህፈት ቤት የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ዘመናዊና ምቹ እንዲሆን የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገለጸ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሳውላ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽህፈት ቤት የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ዘመናዊና ምቹ እንዲሆን የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጿል።
የኦዲት ግኝቶችንና ያለአግባብ የባከነ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስት ሀብት እንዲመለሥ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሠራ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
የሳውላ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽህፈት ቤት ከመንግስትና ከተለያዩ ፕሮጀክቶች የሚመደበው በጀት ህጋዊ የአሠራር ሥርዐትን ተከትሎ በወቅቱ ለታለመላቸው አላማ እንዲውሉ ለማስቻል የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ እሰይ ሰራዊት ገልጸዋል፡፡
በዘርፉ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋና ተቋሙን ለሥራ ምቹ ከማድረግ አኳያ ተጨማሪ የቢሮ ክፍሎች ግንባታ ከማድረግ አንስቶ የክፍያና የግዢ ሰነዶች በአግባቡ ተቀምጠው ለኦዲት ግልጽ እንዲሆኑ ማስቻሉን አስረድተዋል።
የውስጥ ኦዲትን ከማጠናከር አኳያ በሁሉም የሥራ ክፍሎች የኦዲት ባለሙያዎችን በመመደብ ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ያነሱት የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ እሰይ ሰራዊት ይህም አሰራሩ ከሌብነት የጸዳ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል።
ያለ አግባብ የባከነውን የመንግስት ሀብትና 5 ሚሊዮን ብር የኦዲት ግኝት ሙሉ በሙሉ ለማስመለስ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና ከምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር እየተሠራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ዘጋቢ :- አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ