ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአረጋዉያን ያስገነባዉን የመኖሪያ እና እንክብካቤ ማዕከል ስራ አስጀመረ
ማዕከሉ ለ104 አረጋውያን አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተዉ መልዕክት ያስተላለፉት የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር ክፍሌ ወልደሚካኤል፤ አረጋዉያን በወጣትነት ዕድሜያቸዉ በተለያዩ የስራ መስኮች ባላቸዉ እዉቀትና ልምድ ሀገራቸዉን በማገልግል አሁን ላለነዉ ትዉልድ አስተላልፈዋል ብለዋል።
የአረጋዉያን እንክብካቤ ሃገራችን ከምታካሂዳቸዉ የማህበራዊ ጥበቃዎች አንዱ መሆኑን በመግለጽ፤ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለሌሎች መንግስታዊና መንግሰታዊ ላልሆኑ ተቋማት አርዓያነት ያለዉ ተግባር መከወኑን ገልጸዋል።
የዩኒቨርሲቲዉ ሰራተኞችና የአስተዳደር አካላት ከራሳቸዉ ደመወዝ ወርሃዊ ተቆራጭ እያደረጉ ተግባሩን ለዚህ ያበቁት በመሆኑ ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል።
ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ማዕከሉን በእኔነት ስሜት ሊጠብቀዉና ሊንከባከበዉ ይገባል ሲሉ ፕሮፌሰር ክፍሌ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በፕሮግራሙ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አልማዉ ዘዉዴ፣ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ደገላ ኤርገኖን ጨምሮ ሌሎችም ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የሀዋሳ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ለ28ኛ ዙር በመደበኛ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን እጩ መምህራን በዲፕሎማና በሰርተፊኬት ደረጃ በዛሬው ዕለት በሀዋሳ ከተማ አስመርቋል
የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር በምስራቅ ጉራጌ ዞን ምስራቅ መስቃን ወረዳ “ጉዞ ወደ አረንጓዴ ልማት” 14ኛ ዙር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እያካሄደ ይገኛል
ከተረጂነት በመውጣት የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን እንደሚገባ ተገለጸ