ብሄራዊ ቴያትር ከክልሉ 12 ዞኖች ለተውጣጡ ባለ ተሰጥኦዎች ምልመላ በአርባምንጭ ከተማ አካሄደ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ብሔራዊ ቴአትር ለብሔራዊ ጥበብ መዳረሻ” በሚል መሪ ቃል ብሄራዊ ቴያትር ከክልሉ 12 ዞኖች ለተውጣጡ ባለ ተሰጥኦዎች ምልመላ በአርባምንጭ ከተማ አካሂዷል።
በምልመላው ማለፋቸውን ያረጋገጡት ባለተሰጥኦዎች ባገኙት እድል መደሰታቸውን ገልጸው የደቡብ ኢትዮጵያን ክልል እምቅ ጸጋ ለማስተዋወቅ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታሪኩ ኦይቻ በመድረኩ እንዳሉት፣ ቢሮዉ ባህላዊ የኪነ -ጥበብ ሀብቶችን ማልማትና ማስተዋወቅ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ነዉ።
ክልሉ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ጸጋና ቱባ ማንነት ለማስተዋወቅ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች ለመመልመል የኢትዮጲያ ብሔራዊ ቴያትር በአርባምንጭ መገኘቱን ጠቁመዋል።
በክልሉ ከሚገኙ 32 ብሔረሰቦች የተወጣጡ ተሳታፊዎች በዉዝዋዜ፣ ድምፅና ትወና ዘርፍ ተወዳድረው የበለጠ የከወኑ ለብሔራዊ ቴአትር መመመረጠቸውን አቶ ታሪኩ አውስተዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴያትር ዋና ዳይሬክተር አቶ ባርክ ታደሰ ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የበርካታ ቱባ ዕሴቶች ባለቤት መሆኑን አስረድተው ሃገሪቱን በአለም መድረክ ማስተዋወቅ የሚችሉ ልዩ ባለ ተሰጥኦዎችን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል
በኢትዮጲያ ብሔራዊ ቴአትር የጥበባት ምዘናና ስልጠና ዋና አስተባባሪ አርቲስት ካሌብ ዋለልኝ ፤ ኢትዮጲያን ከሚያስተዋዋውቁ በርካታ እሴቶች መካከል የኪነ-ጥበብ አንዱ እንደሆነ ገልፀዋል ።
ይህንን አውን ለማድረግ የኢትዮጲያ ብሔራዊ ቴአትር ከፍተኛ ኃላፊነት የተጣለበት መሆኑን ጠቁመው ለዚህም ከደቡብ ኢትዮጲያ ክልል የድምጽ ፣ የውዝዋዜና የትወና ባለተሰጥኦዎች መመልመላቸውን ጠቁመዋል።
የኢትዮጲያ ብሔራዊ የቴአትር በሰጠው እድል ተወዳድረው ማለፋቸውን ያረጋገጡ ባለተሰጥኦዎች ባገኙት አድል መደሰታቸውን ገልጸው የወከሉትን ብሔርና የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል እምቅ ጸጋን ለማስተዋወቅ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ።
ዘጋቢ ፡ አሰግድ ተረፈ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
የማታ 1፡00 ዜና 24፤ ሀዋሳ፡ ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ሚሻ ወረዳ በኩታ-ገጠም የለማ የስንዴ ማሳ ምልከታ ተደረገ
በታዳጊ ከተሞች የኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭት አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ የመከላከል ስራዎች በትኩረት ማከናወን ይገባል ሲል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አሳሰበ