ሀዋሳ፡ ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሥራ ዕድል ፈጠራ የሚከናወኑ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ እየሠራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ገለፀ።
መምሪያው የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ሥራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት አካሂዷል።
በወቅቱ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አይሶጸ ህሎታ እንዳሉት፥ ክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ተግባርን በትኩረት እያከናወነ ይገኛል፡፡
በክልሉ በሥራ ዕድል ፈጠራ የሚከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ ቢሮው የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጥቀስ የባድርሻ አካላት ትብብር እና ድጋፍም በተገቢው ሊከወን የሚገባው ጉዳይ መሆኑን ነው ኃላፊው የገለፁት።
የዲላ ከተማ ምክትል ከንቲባና ሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታሪኩ በየነ በ2018 መጀሪያው ሩብ ዓመት አፈፃፀም ከአንድ ሺህ ሁለት መቶ በላይ ለሆኑ ሥራ ፈላጊዎች ቋሚና ጊዜያዊ ሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል።
ኃላፊው አክለውም የሥራ ዕድል ከተፈጠረባቸው ዘርፎች ለሚ ኩራ ኢንዱስትሪ ፓርክ፣ ኮሪደር ልማት፣ የከተማ ግብርናና አገልግሎት ዘርፎች ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
በተለያዩ ጊዜያት ተወስደው ያልተመለሱ ውዝፍ ብድሮችን የማስመለስ ተግባርን በትኩረት በማከናወን ተጨማሪ ብድር ለማመቻቸት በትኩረት ይሠራል ብለዋል።
ለሥራ ፈጣሪዎች ምቹ የብድር አቅርቦት እያከናወነ መሆኑን የገለጹት የኦሞ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው በራሶ፥ በዲላ ከተማ በተያዘው በጀት ዓመቱ ለሥራ ፈጣሪ 11 ማህበራት ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር መሰራጨቱን አስታውቀዋል።
በወቅቱ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በከተማው በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ተዘዋውረው የመስክ ምልከታ አድርገዋል።
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
በሥራ ዕድል ፈጠራ የሚከናወኑ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሥራ ዕድል ፈጠራ የሚከናወኑ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ እየሠራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ገለፀ።
መምሪያው የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ሥራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት አካሂዷል።
በወቅቱ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አይሶጸ ህሎታ እንዳሉት፥ ክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ተግባርን በትኩረት እያከናወነ ይገኛል፡፡
በክልሉ በሥራ ዕድል ፈጠራ የሚከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ ቢሮው የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጥቀስ የባድርሻ አካላት ትብብር እና ድጋፍም በተገቢው ሊከወን የሚገባው ጉዳይ መሆኑን ነው ኃላፊው የገለፁት።
የዲላ ከተማ ምክትል ከንቲባና ሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታሪኩ በየነ በ2018 መጀሪያው ሩብ ዓመት አፈፃፀም ከአንድ ሺህ ሁለት መቶ በላይ ለሆኑ ሥራ ፈላጊዎች ቋሚና ጊዜያዊ ሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል።
ኃላፊው አክለውም የሥራ ዕድል ከተፈጠረባቸው ዘርፎች ለሚ ኩራ ኢንዱስትሪ ፓርክ፣ ኮሪደር ልማት፣ የከተማ ግብርናና አገልግሎት ዘርፎች ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
በተለያዩ ጊዜያት ተወስደው ያልተመለሱ ውዝፍ ብድሮችን የማስመለስ ተግባርን በትኩረት በማከናወን ተጨማሪ ብድር ለማመቻቸት በትኩረት ይሠራል ብለዋል።
ለሥራ ፈጣሪዎች ምቹ የብድር አቅርቦት እያከናወነ መሆኑን የገለጹት የኦሞ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው በራሶ፥ በዲላ ከተማ በተያዘው በጀት ዓመቱ ለሥራ ፈጣሪ 11 ማህበራት ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር መሰራጨቱን አስታውቀዋል።
በወቅቱ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በከተማው በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ተዘዋውረው የመስክ ምልከታ አድርገዋል።
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንዳጠናቀቅን ሁሉ የባህር በርን ለማስመለስ የሚደረገውን ጥረት በይበልጥ ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ ተጠቆመ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር እና ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ለኦዲት ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል
ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ