አቶ ገላትያስ ሻሜ የቴፒ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሾሙ
የቴፒ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 13ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ አካሂዷል።
ምክር ቤቱ ባካሄደው በዚህ አስቸኳይ ጉባኤ ላይ አቶ ገላትያስ ሻሜ የቴፒ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሾመዋል።
በምክር ቤቶች አሰራርና አባላት ሥነ ምግባርና ደንብ መሠረት መደበኛ ጉባኤ ከመካሄዱ በፊትም ሆነ በኋላ የምክር ቤቱን ውሳኔ የሚሹ ጉዳዮች ሲኖሩ አስቸኳይ ጉባኤ እንደሚደረግ ተገልጿል።
በዚህም መነሻ የቴፒ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 2ኛ ዙር 13ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ መዘጋጀቱ ተጠቁሟል።
የሸካ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ አለሙ አቅራቢነት አቶ ገላትያስ ሻሜ የቴፒ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው እንዲሾሙ ባቀረቡት መነሻ የምክር ቤት አባላት በሙሉ ድምፅ አጽድቀዋል።
ዘጋቢ: አስቻለው አየለ – ከማሻ ጣቢያችን

More Stories
የፊቼ ጫምባላላ በዓል በሀዋሳ ከተማ በሲዳማ ባሕል አዳራሽ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል
በወራቤ ዩኒቨርስቲ ሴቶችን ወደ አመራርነትና ውሳኔ ሰጪነት ለማምጣት ባለፉት አመታት በተከናወኑ ስራዎች ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸው ተመላከተ
50ኛው የኢትዮጵያ ሴቶች ቀን (ማርች 8) በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ እየተከበረ ነው።