ትክክለኛ መረጃ በመሰብሰብ እና በማደራጀት ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክ አገልግሎት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በአርባ ምንጭ ማዕከል ለ110 ሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው የኢኮኖሚ ድርጅቶች የመስከ ቆጠራ ስልጠና ተጠናቅቋል፡፡
በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ በክልሉ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሔድ ለ25 ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መዝጊያ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ስሜ አንበሴ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ማካሔድ ያሉንን የኢኮኖሚ አቅም በማወቅ ለመተንተንና ለሁለንተናዊ ኢኮኖሚ አቅም ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።
ሰልጣኞች በ25 ቀናት ውስጥ የንድፈ ሐሳብና ተግባር ተኮር ስልጠና የወሰዱ ሲሆን በቂ ዝግጅት መደረጉንም ሀላፊው አስታውቀዋል።
የመረጃ ጥራትን በጠበቀ መልኩ ቆጠራው እንዲካሔድም ሀላፊው አሳስበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ቦጋለ ቦሼ ተከታታይነት ባለው ሁኔታ በሁሉም አቅሞች ዕድገት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው ዘመናዊ የሆነ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ያሉንን አቅሞችን ለማወቅ እና ዕቅድ ዝግጅት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
የመረጃ ሰብሳቢዎች ትክክለኛ እና ተአማኒ መረጃ መሰብሰብ እንዲችሉ መክረዋል።
የጋሞ ዞን አስተዳደር ልዩ አማካሪ አቶ ደረጀ ጳውሎስ የኢኮኖሚ ዘርፎች ለአጠቃላይ አገራዊ ዕድገት ወሳኝ በመሆናቸው በተደራጀ ሁኔታ የናሙና ቆጠራ በማድረግ የዕድገት ደረጃን ለመተንበይ ያግዛል ብለዋል።
ዘጋቢ ወ/ገብርኤል ላቀው ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ