ትክክለኛ መረጃ በመሰብሰብ እና በማደራጀት ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክ አገልግሎት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በአርባ ምንጭ ማዕከል ለ110 ሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው የኢኮኖሚ ድርጅቶች የመስከ ቆጠራ ስልጠና ተጠናቅቋል፡፡
በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ በክልሉ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሔድ ለ25 ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መዝጊያ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ስሜ አንበሴ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ማካሔድ ያሉንን የኢኮኖሚ አቅም በማወቅ ለመተንተንና ለሁለንተናዊ ኢኮኖሚ አቅም ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።
ሰልጣኞች በ25 ቀናት ውስጥ የንድፈ ሐሳብና ተግባር ተኮር ስልጠና የወሰዱ ሲሆን በቂ ዝግጅት መደረጉንም ሀላፊው አስታውቀዋል።
የመረጃ ጥራትን በጠበቀ መልኩ ቆጠራው እንዲካሔድም ሀላፊው አሳስበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ቦጋለ ቦሼ ተከታታይነት ባለው ሁኔታ በሁሉም አቅሞች ዕድገት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው ዘመናዊ የሆነ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ያሉንን አቅሞችን ለማወቅ እና ዕቅድ ዝግጅት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
የመረጃ ሰብሳቢዎች ትክክለኛ እና ተአማኒ መረጃ መሰብሰብ እንዲችሉ መክረዋል።
የጋሞ ዞን አስተዳደር ልዩ አማካሪ አቶ ደረጀ ጳውሎስ የኢኮኖሚ ዘርፎች ለአጠቃላይ አገራዊ ዕድገት ወሳኝ በመሆናቸው በተደራጀ ሁኔታ የናሙና ቆጠራ በማድረግ የዕድገት ደረጃን ለመተንበይ ያግዛል ብለዋል።
ዘጋቢ ወ/ገብርኤል ላቀው ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ