የማህበረሰቡን ሰላም ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ በጉራጌ ዞን በቀቤና ልዩ ወረዳና አጎራባች ቀጠናዎች ኮማንድ ፖስት አስታወቀ
በጉራጌ ዞን፣ በቀቤና ልዩ ወረዳና አጎራባች ቀጠናዎች የተሰሩ የኮማንድ ፖስቱ ስራዎች የሚመለከታቸው የፌደራል፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የኦሮሚያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ እየተገመገመ ይገኛል።
በቀጠናው እስካሁን በኮማንድ ፖስቱ የተሰሩ ስራዎች ግምገማ ሪፖርት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ በአቶ ተመስገን ካሳ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ነው።
በመድረኩም ሜጀር ጀነራል አብድሮ ከድር፣ በተለያዩ የማዕረግ እርከን የሚገኙ የጦር መኮንኖች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ፣ የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ የጅማ፣ የምዕራብ ሸዋና የጉራጌ ዞኖች እንዲሁም የቀቤና ልዩ ወረዳ የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አዱኛ ትዛዙ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ