የማህበረሰቡን ሰላም ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ በጉራጌ ዞን በቀቤና ልዩ ወረዳና አጎራባች ቀጠናዎች ኮማንድ ፖስት አስታወቀ
በጉራጌ ዞን፣ በቀቤና ልዩ ወረዳና አጎራባች ቀጠናዎች የተሰሩ የኮማንድ ፖስቱ ስራዎች የሚመለከታቸው የፌደራል፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የኦሮሚያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ እየተገመገመ ይገኛል።
በቀጠናው እስካሁን በኮማንድ ፖስቱ የተሰሩ ስራዎች ግምገማ ሪፖርት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ በአቶ ተመስገን ካሳ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ነው።
በመድረኩም ሜጀር ጀነራል አብድሮ ከድር፣ በተለያዩ የማዕረግ እርከን የሚገኙ የጦር መኮንኖች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ፣ የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ የጅማ፣ የምዕራብ ሸዋና የጉራጌ ዞኖች እንዲሁም የቀቤና ልዩ ወረዳ የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አዱኛ ትዛዙ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ