የማህበረሰቡን ሰላም ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ በጉራጌ ዞን በቀቤና ልዩ ወረዳና አጎራባች ቀጠናዎች ኮማንድ ፖስት አስታወቀ
በጉራጌ ዞን፣ በቀቤና ልዩ ወረዳና አጎራባች ቀጠናዎች የተሰሩ የኮማንድ ፖስቱ ስራዎች የሚመለከታቸው የፌደራል፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የኦሮሚያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ እየተገመገመ ይገኛል።
በቀጠናው እስካሁን በኮማንድ ፖስቱ የተሰሩ ስራዎች ግምገማ ሪፖርት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ በአቶ ተመስገን ካሳ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ነው።
በመድረኩም ሜጀር ጀነራል አብድሮ ከድር፣ በተለያዩ የማዕረግ እርከን የሚገኙ የጦር መኮንኖች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ፣ የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ የጅማ፣ የምዕራብ ሸዋና የጉራጌ ዞኖች እንዲሁም የቀቤና ልዩ ወረዳ የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አዱኛ ትዛዙ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
በስልጤ ዞን የሚገኘው ሃይረንዚ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2017 የትምህርት ዘመን በሃገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ላይ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እና ውጤቱ እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ላደረጉ መምህራን የማትጊያና የእውቅና ፕሮግራም ተካሄደ
የዋካ ቅርንጫፍ ጣቢያ ወቅታዊና ጥራት ያለውን መረጃ ተደራሽ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እንዲወጣ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ