በአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት እየተሻሻለ መምጣቱን የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ
በሆስፒታሉ የሚሰጠውን አገልግሎት የተሟላ፣ ጥራቱን የጠበቀና ቀልጣፋ በማድረግ የሆስፒታሉን ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሠጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
ለረዥም ዓመታት ከአጥንት ጋር በተያያዘ ለነበረባቸው ህመም ከአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ባገኙት አገልግሎት ከህመም መፈወሳቸውንና በዚህም በእጅጉ መርካታቸውን የገለፁት ወ/ሮ ሽብሬ ከበደ ናቸው፡፡
የአጥንት ህክምና አገልግሎት በአርባምንጭ ሆስፒታል መጀመሩ በተለይ የኢኮኖሚ አቅም ውስንነት ላለባቸው እፎይታ ከመፍጠሩም በተጨማሪ እንግልትና ወጪን እንዳስቀረላቸው ገልፀዋል፡፡
በህፃናት ተኝቶ ህክምና ክፍል ልጃቸውን እያስታመሙ የነበሩትን አቶ ኃይሉ ታደሰ ሆስፒታሉ የሚሰጠው አገልግሎት የተሻለ መሆኑን ጠቁመው አልፎ አልፎ የመድኃኒት እጥረት እንደሚስተዋል ጠቁመዋል፡፡
ከወላድ ክፍል አግኝተን ያነጋገርናቸው ወ/ሮ ዘላለም ገበየሁ በበኩላቸው፤ አገልግሎት አሠጣጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
በፅኑ ህሙማን ክፍል ጠቅላላ ሐኪም ዶ/ር በረከትአብ ከበደ፤ ጥራቱን የጠበቀና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት የተለያዩ ፕሮግራሞችን ተግባራዊ እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ከ4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆን የህብረተሰብ ክፍል የሚሰጠውን አገልግሎት የተሟላ፣ ጥራቱን የጠበቀና ቀልጣፋ በማድረግ የሆስፒታሉን ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሠጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አምባቸው ዱማ ናቸው፡፡
አክለውም በሆስፒታሉ ቀደም ሲል ተጀምረው የተቋረጡ አገልግሎቶችን የማስቀጠል፣ አዳዲሶቹን የማስጀመርና የማዘመን ሥራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
ዘጋቢ:፡ ተነሳ ተረፈ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ