በአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት እየተሻሻለ መምጣቱን የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ
በሆስፒታሉ የሚሰጠውን አገልግሎት የተሟላ፣ ጥራቱን የጠበቀና ቀልጣፋ በማድረግ የሆስፒታሉን ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሠጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
ለረዥም ዓመታት ከአጥንት ጋር በተያያዘ ለነበረባቸው ህመም ከአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ባገኙት አገልግሎት ከህመም መፈወሳቸውንና በዚህም በእጅጉ መርካታቸውን የገለፁት ወ/ሮ ሽብሬ ከበደ ናቸው፡፡
የአጥንት ህክምና አገልግሎት በአርባምንጭ ሆስፒታል መጀመሩ በተለይ የኢኮኖሚ አቅም ውስንነት ላለባቸው እፎይታ ከመፍጠሩም በተጨማሪ እንግልትና ወጪን እንዳስቀረላቸው ገልፀዋል፡፡
በህፃናት ተኝቶ ህክምና ክፍል ልጃቸውን እያስታመሙ የነበሩትን አቶ ኃይሉ ታደሰ ሆስፒታሉ የሚሰጠው አገልግሎት የተሻለ መሆኑን ጠቁመው አልፎ አልፎ የመድኃኒት እጥረት እንደሚስተዋል ጠቁመዋል፡፡
ከወላድ ክፍል አግኝተን ያነጋገርናቸው ወ/ሮ ዘላለም ገበየሁ በበኩላቸው፤ አገልግሎት አሠጣጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
በፅኑ ህሙማን ክፍል ጠቅላላ ሐኪም ዶ/ር በረከትአብ ከበደ፤ ጥራቱን የጠበቀና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት የተለያዩ ፕሮግራሞችን ተግባራዊ እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ከ4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆን የህብረተሰብ ክፍል የሚሰጠውን አገልግሎት የተሟላ፣ ጥራቱን የጠበቀና ቀልጣፋ በማድረግ የሆስፒታሉን ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሠጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አምባቸው ዱማ ናቸው፡፡
አክለውም በሆስፒታሉ ቀደም ሲል ተጀምረው የተቋረጡ አገልግሎቶችን የማስቀጠል፣ አዳዲሶቹን የማስጀመርና የማዘመን ሥራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
ዘጋቢ:፡ ተነሳ ተረፈ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ