“ሂውማን ብሪጅ ኢትዮጵያ” ከተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የ150 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የህክምና ቁሳቁሶችን ለሆስፒታሉ ያበረከተ ሲሆን የህብረተሰቡን የጤና ችግር እንደሚያሻሽሉ ሆስፒታሉ ገልጿል።
የቁሳቁሶቹ መገኘት በማህበረሰቡ ጤና እና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚኖረውን ፋይዳ በተመለከተ የቦንጋ ገብረጻድቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታል ባለሙያዎች አስተያየት ሰጥተዋል።
የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ዋስይሁን መስፍን ባለሙያዎች ከታማሚው ከሚያገኙት መረጃ ባሻገር ቁሳቁሶች የሚሰጡት ውጤት መሠረታዊ ነው ብለዋል።
በሆስፒታሉ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስትና የህሙማን ክፍል አስተባባሪ ዶክተር ሽመልስ አሪቶ፤ የህክምና መሳሪያዎቹ መገኘት የታካሚዎችን እንግልት የሚቀንስና የባለሙያዎችን ተነሳሽነት የሚያሳድግ ነው ብለዋል።
የቦንጋ ገብረጻድቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ፍቅረማርያም ጳውሎስ በበኩላቸው፤ ሆስፒታሉ እቃዎቹን ለመግዛት አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ በነበረበት ወቅት የተገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ዘመናዊ እቃዎቹ የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያቀላጥፉና የህብረተሰቡን የጤና ችግር የሚያሻሽሉ ናቸው ብለዋል።
ዘመናዊና በኤክትሮንክስ ሲስተም የሚሰሩ በመሆናቸው በአጠቃቀም ወቅት ጉዳት እንዳይደርስባቸውና ብክነት እንዳያጋጥም ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል።
ከሆስፒታሉ ተገልጋዮች መካከል ያነጋገርናቸው አቶ ሀብታሙ ኃይሌ በአካባቢው ሪፈራል ሆስፒታሎች ባለመኖራቸው ታካሚዎች ይንገላቱ እንደነበር አስታውሰው፤ ይህ ድጋፍ የጤና አገልግሎቱን እንደሚያሻሽል ተናግረዋል።
ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው የኦፕሬሽን አልጋዎች፣ የአንስቴዥያ ማሽን፣ የቀዶ ጥገና እቃዎች፣ የተለያዩ አልባሳት፣ ዊልቸሮች፣ የተኝቶ ታካሚ አልጋዎች፣ የዐይን ህክምና መሣሪያዎችና ሌሎችም ከተበረከቱ ቁሳቁሶች መካከል ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ አሳምነው አትርሳው – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ