“የታደሰ ጂኦ ስትራቴጂያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ ትጋት” በሚል መሪ ቃል በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ ለሚገኙ የመንግስት ሠራተኞች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ከ3ሺህ በላይ የመንግስት ሠራተኞች በተሳተፉበት በዚህ የስልጠና መድረክ ሀገሪቱ ወደ ነበረችበት ገናናነት ለመመለስ ሁሉም ሠራተኛ የድርሻውን እንዲወጣ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዝ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ የገለፁት የይርጋጨፌ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳዊት የጋ ናቸው፡፡
በከተማው የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ኢትዮጵያ ያለችበት ጂኦ ስትራቴጂያዊ ቁመናን በመረዳት ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር የጋራ ግንዛቤ የተያዘበትና ስኬታማ መድረክ እንደነበረ አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያን ከፍታ በሚጠሉ የውጭ ባዳዎችና የውስጥ ባንዳዎችን በመከላከል የተሰጣቸውን ተግባር በትጋትና በኃላፊነት እንዲፈጽሙ አቶ ዳዊት አሳስበዋል፡፡
የስልጠናው ተሳታፊዎችም ብሔራዊ ጥቅምና ጂኦ ስትራቴጂያዊ ቁመና የጠራ ስዕል የፈጠረ ስልጠና እንደሆነ ገልጸው ሃገሪቱ ከእኛ የምትፈልገውን ሁሉ ለመስጠት ቁርጠኛ ነን ብለዋል።
ዘጋቢ፡ አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የፍትህ ስርዓቱን ተደራሽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተሰራ ነዉ – የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን ሴቶች በግንባር ቀደምነት በመሳተፍ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው