የየኪ ወረዳ አስተዳደር በበኩሉ ዘንድሮ ብቻ 5 ሺ ሄክታር ያረጁ ቡናዎችን በማስጎንደል በዘመናዊ ቡና ለማስተካት አቅዶ እየሰራ መሆኑን አስታዉቋል።
በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር የቴፒ ብሄራዊ ቅመማ ቅመም ማዕከል የሰጣቸዉን ምርጥ የቡና ችግኝ በዘመናዊ አሰራር በማልማታቸዉ በተከሉ በአንድ አመት ጊዜ ዉስጥ ቡናቸዉ ምርት መስጠት መጀመሩን ነዉ በየኪ ወረዳ አላሞ ቀበሌ ሞደል ወጣት አርሶ አደር ይንገስ ጌታቸዉና ብርሃኑ ጌታቸዉ የተናገሩት።
አርሶ አደሮቹ ከዚህም በላቀ ደረጃ በጥራትና በሰፋት ቡናን በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እንዲችሉ አሁን ላይ ያለባቸዉን የመሬት አቅርቦች ችግር ሚመለከተዉ አካል እንዲፈታላቸዉ ጠይቀዋል።
ሁሉም አርሶ አደሮችና ሚመለከታቸዉ አካላት በሙሉ ያረጁና ምርታማነታቸው ያበቃ ቡናዎችን ምረታማነታቸዉ በመርምር ማዕከል በተረጋገጡ በመተካቱ ረገድ ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር የቴፒ ብሄራዊ ቅመማ ቅመም ማዕከል ዳይሬክተር ዶክተር ደረጀ ቱሉ አሳስበዋል።
የየኪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ተሰማ በበኩላቸዉ፤ በወረዳዉ ካለዉ ቡና ሽፋን አብዛኛዉ ያረጀ በመሆኑ ዘንድሮ ብቻ 5 ሺ ሄክታር በማስጎንደል በዘመናዊና ምርታማ ቡናዎች ለመተካት መታቀዱን ገልጸዉ፤ በተለይም በቡና ጥራት ማስጠበቅ ላይ ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ አሳስበዋል።
የወጣቶቹ የመሬት አቅርቦት ጥያቄ በሚፈታበትም ዙሪያ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ይሰራል ብለዋል።
ዘጋቢ: ጌትነት ገረመዉ – ከማሻ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ