የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በደማቅ ስነ ስርዓት በሣጃ ከተማ እየተከበረ ነው
ሄቦ ከጭጋግና ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ምዕራፍ መሸጋገሪያ በዓል ነው።
የሄቦ በዓል የአዲስ ዓመት ብርሃን ማብሰሪያ፣ በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው ርቀው የሚኖሩ ከቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ታላቅ በዓል ነው።
በሄቦ የዘመን መለወጫ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የዕለቱ የክብር እንግዳ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት ኤርሲኖ አቡሬ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና የመንግስ ተጠሪና የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ አቶ ይሁን አሰፋ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ፣ በበዓሉ ላይ እየተሳተፉ ነው።
ከተለያዩ የክልሉ አከባቢዎችና ከሦስቱም የዞኑ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የብሔረሰቡ ተወላጆች፣ ባለሀብቶች፣ የትምህርት አመራሮች፣ መምህራን፣ ተማሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የንግድ ማህበረሰብ ተወካዮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ ባለድርሻ አካላት እየሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ