የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በደማቅ ስነ ስርዓት በሣጃ ከተማ እየተከበረ ነው
ሄቦ ከጭጋግና ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ምዕራፍ መሸጋገሪያ በዓል ነው።
የሄቦ በዓል የአዲስ ዓመት ብርሃን ማብሰሪያ፣ በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው ርቀው የሚኖሩ ከቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ታላቅ በዓል ነው።
በሄቦ የዘመን መለወጫ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የዕለቱ የክብር እንግዳ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት ኤርሲኖ አቡሬ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና የመንግስ ተጠሪና የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ አቶ ይሁን አሰፋ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ፣ በበዓሉ ላይ እየተሳተፉ ነው።
ከተለያዩ የክልሉ አከባቢዎችና ከሦስቱም የዞኑ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የብሔረሰቡ ተወላጆች፣ ባለሀብቶች፣ የትምህርት አመራሮች፣ መምህራን፣ ተማሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የንግድ ማህበረሰብ ተወካዮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ ባለድርሻ አካላት እየሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ