የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሠራተኞች እና በኣሪ ዞን ስር ባሉ መዋቅሮች የሚገኙ የመንግስት ሠራተኞች “ብሔራዊ ጥቅምና ጂኦ ስትራቴጂ ቁመና” በሚል ርዕስ ሰነድ ቀርቦ ተወያዩ
ሀዋሳ፡ መስከረም 21/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ብሔራዊ ጥቅምና ጂኦ ስትራቴጂ ቁመና” በሚል ርዕስ ሰነድ ቀርቦ በዚሁ መነሻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሠራተኞች እና በኣሪ ዞን ስር ባሉ መዋቅሮች የሚገኙ የመንግስት ሠራተኞች በተለያየ ቡድን ተከፋፍለው ተወያይተዋል።
መድረኩን የመሩ አካላትም ለተወያዮች በየመድረኮቹ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የሀገር ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ አኳያ፣ ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎችን በመገንዘብ የመንግስት ሠራተኞች በተሰማሩበት ቦታ ለእናት ሀገር ለውጥና ብልፅግና ተግተው መሥራት እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል።
አሁን ላይ ያለው ሀገራዊ ሁኔታ ከመንግስት ሠራተኞች ልዩ ቁርጠኝነትና ትጋትን የሚጠይቅ መሆኑን መድረኩን የያዙ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች ገልፀዋል።
በተለይ ብሔራዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ አኳያ ሁሉም የጠራ ግንዛቤ በመያዝ የሀገር ሉዓላዊነትን ማስጠበቅ ከሁሉም የሚጠበቅ የዜግነት ሀላፊነት ነው ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎችም ከቀረበው ሰነድ መነሻ የግልፀኝነት ጥያቄዎችን ያነሱ ሲሆን ምላሽ ተሰጥቶባቸው የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
ሁላችንም ለሀገራችን ለውጥና ሉዓላዊነት ጠንክረን እንሠራለን ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ