‎ለመኸር እርሻ ከ82 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የቡርጂ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ

‎ለመኸር እርሻ ከ82 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የቡርጂ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ

‎የቡርጂ ዞን ግብርና መምሪያ የአዝርዕት ሰብሎች ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ቦጋለ ጅራ 2017/2018 መኸር እርሻ 83 ሺህ 5 መቶ 55 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን አቅደው ከዚህም ውስጥ 82 ሺህ 3 መቶ 63 ሄክታር መሬት በዋና ዋና ሰብሎች መሸፈናቸውን አንስተው ከተዘሩ ሰብሎችም 70 በመቶ ቦሎቄ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ከተዘራው ሰብል ከ1 ሚሊዬን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚገመት ቡድን መሪው አንስተዋል።

‎የነፍሳት ተባይ፣ የበሽታ ተባይና አረም ምርትን የሚጎዱ ስለሆኑ አርሶ አደሩ አረሙን በወቅቱ በማንሳት ተባይ ከተከሰተም ለግብርና ባለሙያዎች በማሳወቅ ሁል ጊዜ ማሳቸውን ከትትል እንዲያደርጉ አቶ ቦጋለ አሳስበዋል።

‎የወረዳው ጉዴ ቀበሌ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ተመስገን ፀቤ በበኩላቸው፤ የተለያዩ ግብዓቶችን በማቅረብና ግንዛቤ በማስጨበጥ ለአርሶ አደሮች ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

‎ካነጋገርናቸው አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር አደን ጋሮ፣ ኦዳ ጡኮ እና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት አሁን ማሳ ላይ ያለው ሰብል ጥሩ ደረጃ በመሆኑ የአርም ቁጥጥር ስራ ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል።

‎ዘጋቢ፡ ቦጋለ ሉሳ – ከይርጋ ጨፌ ጣቢያችን