በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ ባለፈው ዓመት የተከናወኑ ተግባራት በርካታ ችግሮችን የፈቱ አንደነበሩ ተገለፀ
በወረዳው የ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ መድረክ ተካሂዷል።
መድረኩን ያስጀመሩት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔ፤ በእያንዳንዱ አገልግሎት መስክ በንቃት በመሳተፍ የላቀ ውጤት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ያበረከቱትን አካላት አመስግነው፤ የተጀመሩ በጎ ተግባራትን ለማስቀጠል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም አሳስበዋል።
የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ አየለ፤ ወጣቶችን 18 በሚሆኑ ዘርፎች በማሳተፍ ችግር ፈቺ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል።
በአረንጓዴ አሻራ የግብርና ሥራዎች ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ ከታቀደው በላይ ማከናወን መቻሉን ጠቅሰው፤ 5 መቶ 18 የሚሆኑ የአቅመ ደካሞችን ቤቶች ግንባታና ጥገና መደረጉን ገልጸዋል።
55 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች በተሳተፈበት በክረምቱ መርሀግብር 136 ሺህ የሚሆኑ ወገኖችን ተጠቃሚ በማድረግ አገልግሎቱ በገንዘብ ሲሰላ 58 ሚሊዮን ብር እንደሚሆንም ገልጸዋል።
በአገልግሎቱ ከተሳተፉት ወጣቶች መካከል ወጣት መክብብ ደሳለኝና ኃይሉ ተሰማ፤ ማንም ሳያስገድዳቸው በራሳቸው ፈቃድ በተለያዩ ዘርፎች በመሰማራት ሲያገለግሉ መቆየታቸውን ገልጸው በዋጋ የማይተመን እርካታ ማግኘታቸውን አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ አማኑኤል ትዕግሥቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ