በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ ባለፈው ዓመት የተከናወኑ ተግባራት በርካታ ችግሮችን የፈቱ አንደነበሩ ተገለፀ
በወረዳው የ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ መድረክ ተካሂዷል።
መድረኩን ያስጀመሩት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔ፤ በእያንዳንዱ አገልግሎት መስክ በንቃት በመሳተፍ የላቀ ውጤት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ያበረከቱትን አካላት አመስግነው፤ የተጀመሩ በጎ ተግባራትን ለማስቀጠል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም አሳስበዋል።
የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ አየለ፤ ወጣቶችን 18 በሚሆኑ ዘርፎች በማሳተፍ ችግር ፈቺ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል።
በአረንጓዴ አሻራ የግብርና ሥራዎች ከ23 ሺህ በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ ከታቀደው በላይ ማከናወን መቻሉን ጠቅሰው፤ 5 መቶ 18 የሚሆኑ የአቅመ ደካሞችን ቤቶች ግንባታና ጥገና መደረጉን ገልጸዋል።
55 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች በተሳተፈበት በክረምቱ መርሀግብር 136 ሺህ የሚሆኑ ወገኖችን ተጠቃሚ በማድረግ አገልግሎቱ በገንዘብ ሲሰላ 58 ሚሊዮን ብር እንደሚሆንም ገልጸዋል።
በአገልግሎቱ ከተሳተፉት ወጣቶች መካከል ወጣት መክብብ ደሳለኝና ኃይሉ ተሰማ፤ ማንም ሳያስገድዳቸው በራሳቸው ፈቃድ በተለያዩ ዘርፎች በመሰማራት ሲያገለግሉ መቆየታቸውን ገልጸው በዋጋ የማይተመን እርካታ ማግኘታቸውን አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ አማኑኤል ትዕግሥቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ