ታራሚዎች ሰብዓዊ መብታቸው ተከብሮ በስነ ምግባርና በሙያ ታንፀው በቴክኖሎጂ ሽግግር ብቁ ዜጎች እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ መስከረም 20/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ታራሚዎች ሰብዓዊ መብታቸው ተከብሮ በስነ ምግባርና በሙያ ታንፀው በቴክኖሎጂ ሽግግር ብቁ ዜጎች እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም አስታወቀ።
የህግ ታራሚዎችም በተቋሙ በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ነሬሬ፤ ታራሚዎች ሰብአዊ መብታቸው ተከብሮ እነሱም የሌሎችን መብት አክብረው በስነ ምግባርና በሙያ ታንፀው በቴክኖሎጂ ሽግግር ብቁ ዜጎች እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም የህግ ታራሚዎች በተደራጁበት የስራ መስክ የሚያመርቱትን ምርት ለማህበረሰቡ በማቅረብ የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ ከጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጋር በመነጋገር የመሸጫ ቦታ ለማመቻቸት እየተሰራ እንዳለም አስረድተዋል።
በተቋሙ የማረምና ማነፅ ተሀድሶ ልማት ዲቪዥን አስተባባሪ ኮማንደር ደመቀ እንዳለ፤ በ2018 ዓ.ም ታራሚዎች በማሽነሪ፣ በጋርመንት፣ በእደ ጥበብ፣ በሽመናና በሌሎች የሙያ መስኮች በቴክኒክና ሙያ ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግና በማህበር በማደራጀት የመስሪያ ቦታ ተመቻችቶላቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የህግ ታራሚዎች በሰጡት አስተያየት በማረሚያ ቆይታቸው የባህሪ ለውጥ አምጥተው በተቋሙ በተፈጠረላቸው የስራ እድል ተጠቃሚ በመሆን የእርምት ጊዜያቸውን አጠናቀው ከማህበረሰቡ ጋር በሚቀላቀሉበት ጊዜ በሰለጡኑበት የሙያ ዘርፍ በመሰማራት ሰላማዊና አምራች ሀይል እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ በናወርቅ መንግስቱ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ