የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ በተለያየ ወንጀል ተጠርጥረው ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የመስቀል በአልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋራ
ተጠርጣሪዎችም የከተማው ፖሊስ ላበረከተው አስተዋፅኦ አመስግነዋል።
የመስቀል በአል በአደባባይ ከሚከበሩ አበይት በዓላት መካከል ቀዳሚው መሆኑ ይታወቃል።
የአርባ ምንጭ ከተማ ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ጥሩነሽ ተስፋዬ በማዕድ ማጋራት መርሀ ግብሩ ተገኝተው ለተጠርጣሪዎች ባስተላለፉት መልእክት፤ የመስቀል በዓል የተጣላ የሚታረቅበትና በአብሮነት የሚከበር በአል በመሆኑ የከተማው ፖሊስ ላሳየው ፍቅርና አክብሮት አመስግነዋል።
በጋሞ ብሔረሰብ ዘንድ ለእንስሳትም ለሰው የጥጋብ ወቅት ተብሎ የመስቀል በአል እንደሚታመን አብራርተው፤ ለተጠርጣሪዎች ማዕድ በማጋራት አብሮነታቸውን ያሳዩ የፖሊስ አባላትን ልምድ በመቅሰም በሌሎችም ተቋማት ሊለመድ ይገባል ብለዋል።
የከተማው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገበየሁ ፃራ፤ የወጣቱን ስብዕና በመገንባት ሰላም ወዳድ እንዲሆን በማነፅ ረገድ የከተማው ፖሊስ ጠንካራ ስራ መስራቱን ገልፀው በጣቢያው የሚገኙ ተጠርጣሪዎች የወንጀል አስከፊነትን በመረዳትና ወንጀልን በመከላከል ረገድ ከፖሊስ ጎን በመቆም የልማት ተሳታፊ እንዲሆኑ አደራ ብለዋል፡፡
የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ክበበው አዳል ወንጀል ማህበራዊ ክስተት በመሆኑ በየትኛው አጋጣሚ ተጠርጥረው በህግ ጥላ ስር የሚገኙ ወገኖች እኛ በምንሰጠው ፍቅር ደስተኛ እንዲሆኑና ወንጀልን የሚፀየፉና ሰላም ወዳድ እንዲሆኑ በማሰብ የመስቀል በዓልን ከተጠርጣሪዎች ጋር ማዕድ በማጋራት በጋራ ማሳለፋቸውን አስታውቀዋል።
በፖሊስ ጣቢያው የሚገኙ ተጠርጣሪዎች በተደረገላቸው አብሮነት መደሰታቸውን ገልፀው፤ ከጣቢያው ወጥተው ህብረተሰቡን ሲቀላቀሉ ፖሊስንና ህብረተሰቡን ለመካስ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
የሳሮ እና ዳሮስ ኢንተርናሽናል ሆቴል ስራ አስኪያጆች ከከተማው ፖሊስ ጋር በአብሮነት ለተጠርጣሪዎች ማዕድ በማጋራታቸው መደሰታቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ