በአርባምንጭ ከተማ የመስቀል ደመራ በአል በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ነው።
የመስቀል ደመራ በአል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከሚከበሩ በአላት መካከል አንዱ ሲሆን በአብሮነትና በጋራ የሚከበር ታላቅ በአል መሆኑን የአርባ ምንጭ ከተማ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበችው የማይዳሰሱ ቅርሶች ውስጥ አንዱ በመሆኑ ከሃማኖታዊ ስርአቱ ባሻገር ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክርና ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ምዕመናኑ ገልፀዋል።
ይህንን ባህላዊና ሀይማኖታዊ ይዘት ያለውን ታላቅ በአል ሳይበረዝ ለትውልድ ለማስተላለፍ ሁሉም ሃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አስታውቀዋል።
በአርባምንጭ ከተማ የደመራ በአል ሀይማኖታዊ ስርአቱን ጠብቆ በድምቀት አየተከበረ ይገኛል።
ዘጋቢ፡- ገነት መኮንን

More Stories
የባስኬቶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጡን ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ አስፈላጊውን ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ገለጸ
ብልጽግናን ለማረጋገጥ የፖሊስ አመራር እና አባላትን አቅም ማሳደግ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
ህዳር 29 ለሚከበረው የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል የአሰልጣኞች ሥልጠናና ማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ በካራት ከተማ እየተካሄ ይገኛል