በአርባምንጭ ከተማ የመስቀል ደመራ በአል በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ነው።
የመስቀል ደመራ በአል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከሚከበሩ በአላት መካከል አንዱ ሲሆን በአብሮነትና በጋራ የሚከበር ታላቅ በአል መሆኑን የአርባ ምንጭ ከተማ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበችው የማይዳሰሱ ቅርሶች ውስጥ አንዱ በመሆኑ ከሃማኖታዊ ስርአቱ ባሻገር ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክርና ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ምዕመናኑ ገልፀዋል።
ይህንን ባህላዊና ሀይማኖታዊ ይዘት ያለውን ታላቅ በአል ሳይበረዝ ለትውልድ ለማስተላለፍ ሁሉም ሃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አስታውቀዋል።
በአርባምንጭ ከተማ የደመራ በአል ሀይማኖታዊ ስርአቱን ጠብቆ በድምቀት አየተከበረ ይገኛል።
ዘጋቢ፡- ገነት መኮንን

More Stories
ስፖርተኞች መልካም ስብእና ተላብሰው ውድድራቸውን እያካሄዱ እንደሚገኙ የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ
የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከል በሚደረገው አገራዊ ጥረት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅምና መብት በማስጠበቅ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ