በአርባምንጭ ከተማ የመስቀል ደመራ በአል በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ነው።
የመስቀል ደመራ በአል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከሚከበሩ በአላት መካከል አንዱ ሲሆን በአብሮነትና በጋራ የሚከበር ታላቅ በአል መሆኑን የአርባ ምንጭ ከተማ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበችው የማይዳሰሱ ቅርሶች ውስጥ አንዱ በመሆኑ ከሃማኖታዊ ስርአቱ ባሻገር ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክርና ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ምዕመናኑ ገልፀዋል።
ይህንን ባህላዊና ሀይማኖታዊ ይዘት ያለውን ታላቅ በአል ሳይበረዝ ለትውልድ ለማስተላለፍ ሁሉም ሃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አስታውቀዋል።
በአርባምንጭ ከተማ የደመራ በአል ሀይማኖታዊ ስርአቱን ጠብቆ በድምቀት አየተከበረ ይገኛል።
ዘጋቢ፡- ገነት መኮንን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ