በአርባምንጭ ከተማ የመስቀል ደመራ በአል በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ነው።
የመስቀል ደመራ በአል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከሚከበሩ በአላት መካከል አንዱ ሲሆን በአብሮነትና በጋራ የሚከበር ታላቅ በአል መሆኑን የአርባ ምንጭ ከተማ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበችው የማይዳሰሱ ቅርሶች ውስጥ አንዱ በመሆኑ ከሃማኖታዊ ስርአቱ ባሻገር ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክርና ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ምዕመናኑ ገልፀዋል።
ይህንን ባህላዊና ሀይማኖታዊ ይዘት ያለውን ታላቅ በአል ሳይበረዝ ለትውልድ ለማስተላለፍ ሁሉም ሃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አስታውቀዋል።
በአርባምንጭ ከተማ የደመራ በአል ሀይማኖታዊ ስርአቱን ጠብቆ በድምቀት አየተከበረ ይገኛል።
ዘጋቢ፡- ገነት መኮንን
More Stories
የተለያዩ የህክምና መድሀኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት መቻላቸውን በሚዛን አማን ከተማ በማህበረሰብ አቀፍ ፋርማሲ ሲገለገሉ ያገኘናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ገለፁ
የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በደማቅ ስነ ስርዓት በሣጃ ከተማ እየተከበረ ነው
በክረምት ወራት የታየውን ትጋት በበጋውም ለመድገም ቁርጠኞች መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ