የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የመስቀልን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ!
እንኳን ለብረሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ!፤ አደረሰን! እያልኩ ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡
ባለብዙ ቀለም፣ መስኩ ለምለም፣ ዜጎች ለአዳዲስ ሰኬቶች የሚነሳሱበት የተስፋና የብርሃን ወቅት በሆነዉ ወርሃ መስከረም የሚከበረው የመስቀል በዓል ልዩ ድምቀት ያለዉና በሃይማኖታዊና ማህራዊ እሴቶችና ትሩፋቶች የታጀበ ነዉ።
ተፈጥሮ ምድርን ደማቅና ዉብ አድርጎ በሚያሸበርቅበት፣ የአዲስ ዓመት ማግስት የሚከበረዉ የመስቀል በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮዉና ማህበራዊ ትዉፊቶቹ ለአዳዲስ ሰኬቶች የሚያነሳሱ ናቸዉ።
በዓሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም ከሃይማኖታዊ እሴቶቹ ባሻገር ማህበራዊ ትሩፋቶቹ በርካታ ናቸዉ።
ተራርቀዉ የሠነበቱ ቤተሰቦች፣ ተገናኝተዉ ቤተሰባዊ ፍቅራቸዉን የሚወጡበት፣ ሐሴታቸዉን የሚገልፁበት ነዉ።
የተስፋ ብርሃን፣ የፅናት፣ የአሸናፊነትና የመስዋዕትነት ምልክት የሆነዉ የመስቀል በዓል የአብሮነት፣ የተስፋና የትጋት እሴቶችን እንድናጠናክር የሚያግዝ ነዉ።
በዓሉ የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት፣ ለሠላምና ለልማት ግንባታ በአጠቃላይ ለሁለንተናዊ ብልጽግና በጋራ ለመትጋት የምንነሳሰበት እንዲሆን እመኛለሁ።
መልካም የመስቀል በዓል!
አመሠግናለሁ !

More Stories
በከምባታ ዞን የሺንሽቾ ከተማ የመሠረተ ልማት ተግባራት በማጠናከር የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ86 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ
የተቀናጀ የመሬት አያያዝ ፖሊሲ የቡና ምርታማነትን እንደሚያሳድግ ተገለፀ