የጋዜጠኞችን አቅም በማጎልበት የመፈጸም አቅም ማሳደግ እንደሚገባ ተገለጸ

የጋዜጠኞችን አቅም በማጎልበት የመፈጸም አቅም ማሳደግ እንደሚገባ ተገለጸ

‎ሀዋሳ፡ መስከረም 14/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የጋዜጠኞችን አቅም በማጎልበት በዜና፣ ፕሮግራም እና በአርትኦት ስነ-ምግባር ዙሪያ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

የአርባምንጭ ኤፍኤም 90.9 ከተመሠረተበት ሰኔ 2001 ዓ.ም ጀምሮ በ 9 የብሔረሰብ ቋንቋዎች የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት ለማረጋገጥ እና ለህብረተሰቡ በመድረስ ሁሉን አቀፍ ለውጥ እንዲመዘገብ እየሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።

‎የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ም/ስራ አስኪያጅና ይዘት ስራዎች ዘርፍ አስተባባሪ አቶ በኃይሉ ሙሉጌታ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ለተከታታይ 3 ቀናት በዜና እና ፕሮግራም አዘገጃጀት እንዲሁም በአርትኦት ሥነ-ምግባር ዙሪያ የሚሰጠውን ስልጠና ጋዜጠኞች በንቃት ተከታትለው የተሻለ ዕውቀት እንዲጨብጡ አሳስበዋል።

‎የደሬቴድ አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራአስኪያጅ አቶ ጉጃ ጉሜ በበኩላቸው በ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የመፈጸም አቅም ለመገንባት ተቋሙ የያዘውን እቅድ እውን ለማድረግ የሚሰጥ ስልጠና በመሆኑ አርታኢያንና አዘጋጆች ከስልጠናው ጉድለታቸውን የሚሞሉበት እንደሚሆን እምነታቸውን ገልፀዋል ።

‎የማስፈጸም አቅም ማሻሻል የሚቻለው በልምድ እና ዕውቀት የበቁ ባለሞያዎችን መፍጠር ሲቻል መሆኑን አብራርተዋል።

‎በሬዲዮ ዜና ፣ ፕሮግራም እንዲሁም ከቴሌቪዥን ዜና እና ፕሮግራም አዘገጃጀት እና አርትኦት እንዲሁም ሥነ-ምግባር አንፃር የሚስተዋሉ ውስንነቶችን ለማረም የውስጥ አቅምን አሟጦ መጠቀም አዋጭ መንገድ ነው ብለዋል።

‎ተቋሙ የውስጥ አቅምን ተጠቅሞ በሚሰጠው ስልጠናን ሰልጣኙ በአጽንኦት እንዲከታተል አቶ ጉጃ አሳስበዋል።

‎ዘጋቢ ፡ አሰግድ ተረፈ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን