የጎፋ ጋዜ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ በዓል በጋራ መከበሩ አብሮነትንና የእርስ በርስ ትስስርን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተገለጸ
ሀዋሳ፡ መስከረም 14/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጎፋ ጋዜ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ በዓል መከበሩ አብሮነትንና የእርስ በርስ ትስስርን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑን የበዓሉ ተሳታፊዎች ገለጹ።
በዓሉ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ዓመት በመሸጋገራቸው አምላካቸውን የሚያመሰግኑበት፣ ለሀገራቸው እና ለሕዝባቸው ሠላምና ጠንነትን፣ ጥጋብ እና ደስታ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን በመግለጽ የሚያከብሩት በዓል ነው።
በበዓሉ ላይ የተገኙ የዞኑ ተወላጆች በሰጡት አስተያዬት በዓሉ ከአሮጌ ወደ አዲስ ዓመት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን የመሸጋገር ምልክት መሆኑን ገልጸው፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የአንድነት ተምሳሌት ነው ብለዋል።
የዘንድሮው በዓል በዶ/ር ዮናታን ጀረነ እና በዶ/ር ቦሻ ቦንበ የተዘጋጀው የጎፋና ኦይዳ ህዝቦች ባህልና ታሪክ መጽሐፍ በተመረቀበት ወቅት መከበሩ ልዩ ያደርገዋል ሲሉ ገልጸዋል።
ከአጎራባች ዞኖች የተገኙ ተጋባዥ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያዬት በዓሉ አንድነትንና አብሮነትን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
ተጋባዥ እንግዶች ለጎፋና ኦይዳ ህዝቦች አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የፍቅር፣ የይቅርታ፣ የአብሮነት፣ የመቻቻልና የመከባበር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
የወረዳውን ዕድገት ለማፋጠን የተጀመሩ የመሰረተ ልማት ተቋማት ሊፋጠኑ ይገባል
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በወ/ሮ አዱኛ አዛዥ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ