የጎፋ ጋዜ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ በዓል በጋራ መከበሩ አብሮነትንና የእርስ በርስ ትስስርን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተገለጸ
ሀዋሳ፡ መስከረም 14/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጎፋ ጋዜ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ በዓል መከበሩ አብሮነትንና የእርስ በርስ ትስስርን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑን የበዓሉ ተሳታፊዎች ገለጹ።
በዓሉ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ዓመት በመሸጋገራቸው አምላካቸውን የሚያመሰግኑበት፣ ለሀገራቸው እና ለሕዝባቸው ሠላምና ጠንነትን፣ ጥጋብ እና ደስታ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን በመግለጽ የሚያከብሩት በዓል ነው።
በበዓሉ ላይ የተገኙ የዞኑ ተወላጆች በሰጡት አስተያዬት በዓሉ ከአሮጌ ወደ አዲስ ዓመት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን የመሸጋገር ምልክት መሆኑን ገልጸው፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የአንድነት ተምሳሌት ነው ብለዋል።
የዘንድሮው በዓል በዶ/ር ዮናታን ጀረነ እና በዶ/ር ቦሻ ቦንበ የተዘጋጀው የጎፋና ኦይዳ ህዝቦች ባህልና ታሪክ መጽሐፍ በተመረቀበት ወቅት መከበሩ ልዩ ያደርገዋል ሲሉ ገልጸዋል።
ከአጎራባች ዞኖች የተገኙ ተጋባዥ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያዬት በዓሉ አንድነትንና አብሮነትን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
ተጋባዥ እንግዶች ለጎፋና ኦይዳ ህዝቦች አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የፍቅር፣ የይቅርታ፣ የአብሮነት፣ የመቻቻልና የመከባበር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ