የጠምባሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “መሳላ” በዓል በሙዱላ ከተማ እየተከበረ ነዉ
ሀዋሳ፡ መስከረም 11/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “መሳላ” በዓል ለመጀመሪያ ጊዜ በሙዱላ ከተማ በአደባባይ እየተከበረ ይገኛል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሀዲ፡ የክልልና የልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
አመራሮቹ የፎቶ አዉደ ርዕይንና የጠምባሮ ብሔረሰብ ባህላዊ ምግቦችንም ጎብኝተዋል፡፡
ከአጎራባች መዋቅሮች በዓሉን ለመታደም የመጡ እንግዶችም ለልዩ ወረዳዉ የሰንጋ ስጦታ በርክተዋል፡፡
የጠምባሮ መሳላ በዓል የጠምባሮ ብሔረሰብ አዲስ ዓመቱን የሚቀበልበት በዓል ነዉ።
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ