የጠምባሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “መሳላ” በዓል በሙዱላ ከተማ እየተከበረ ነዉ
ሀዋሳ፡ መስከረም 11/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “መሳላ” በዓል ለመጀመሪያ ጊዜ በሙዱላ ከተማ በአደባባይ እየተከበረ ይገኛል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሀዲ፡ የክልልና የልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
አመራሮቹ የፎቶ አዉደ ርዕይንና የጠምባሮ ብሔረሰብ ባህላዊ ምግቦችንም ጎብኝተዋል፡፡
ከአጎራባች መዋቅሮች በዓሉን ለመታደም የመጡ እንግዶችም ለልዩ ወረዳዉ የሰንጋ ስጦታ በርክተዋል፡፡
የጠምባሮ መሳላ በዓል የጠምባሮ ብሔረሰብ አዲስ ዓመቱን የሚቀበልበት በዓል ነዉ።
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ

More Stories
በስራ ቦታቸው ላይ የህፃናት ማቆያ ማዕከል መቋቋሙ ስራቸውን በአግባቡ ለማከናወን እንዳስቻላቸው የማእከሉ ተጠቃሚ እናቶች ገለፁ
ለግብርናው እድገት መንግስት ከሚያደርገው ጥረት ጎን ለጎን የግብርና አጋር አካላት ድጋፍ የማይተካ ሚና እንዳለው የጎፋ ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ
በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የጥምቀት በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከብሯል