የጠምባሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “መሳላ” በዓል በሙዱላ ከተማ እየተከበረ ነዉ
ሀዋሳ፡ መስከረም 11/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “መሳላ” በዓል ለመጀመሪያ ጊዜ በሙዱላ ከተማ በአደባባይ እየተከበረ ይገኛል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሀዲ፡ የክልልና የልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
አመራሮቹ የፎቶ አዉደ ርዕይንና የጠምባሮ ብሔረሰብ ባህላዊ ምግቦችንም ጎብኝተዋል፡፡
ከአጎራባች መዋቅሮች በዓሉን ለመታደም የመጡ እንግዶችም ለልዩ ወረዳዉ የሰንጋ ስጦታ በርክተዋል፡፡
የጠምባሮ መሳላ በዓል የጠምባሮ ብሔረሰብ አዲስ ዓመቱን የሚቀበልበት በዓል ነዉ።
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ

More Stories
የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንዳጠናቀቅን ሁሉ የባህር በርን ለማስመለስ የሚደረገውን ጥረት በይበልጥ ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ ተጠቆመ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር እና ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ለኦዲት ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል
ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ