የጠምባሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “መሳላ” በዓል በሙዱላ ከተማ እየተከበረ ነዉ
ሀዋሳ፡ መስከረም 11/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “መሳላ” በዓል ለመጀመሪያ ጊዜ በሙዱላ ከተማ በአደባባይ እየተከበረ ይገኛል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሀዲ፡ የክልልና የልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
አመራሮቹ የፎቶ አዉደ ርዕይንና የጠምባሮ ብሔረሰብ ባህላዊ ምግቦችንም ጎብኝተዋል፡፡
ከአጎራባች መዋቅሮች በዓሉን ለመታደም የመጡ እንግዶችም ለልዩ ወረዳዉ የሰንጋ ስጦታ በርክተዋል፡፡
የጠምባሮ መሳላ በዓል የጠምባሮ ብሔረሰብ አዲስ ዓመቱን የሚቀበልበት በዓል ነዉ።
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ