የኣሪ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ የፐብሊክ ሰረቫንት ቀንን በማስመልከት በአፈፃፀማቸው የተሻሉ ተቋማትና ግለሰቦች ዕውቅና ተሰጣቸው
ሠራተኞችን መመዘን፣ ማበረታታትና መደገፍ ብሎም ማሰልጠን በሚሠሩባቸው ዘርፎች በተሻለ ሞራል ሥራቸውን እንዲከውኑ ያስችላል፤ ይህ ደግሞ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ጭምር ነው ያሉት የኣሪ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ አቶ አሸብር ጋልሶ ናቸው።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ እንደገለፁት፤ ፐብሊክ ሰርቫንት በሀገሪቱ ለውጥ ሂደት ውስጥ አይተኬ ሚና አላቸው።
በበቂ ሁኔታ ሠራተኞችና ሀብት በሌለበት በውስን ባለሙያዎች በጋራ ቅንጅት የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ በቁርጠኝነት የሠሩ አካላትን አበረታትው፤ በቀጣይም ጠንክረው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
ሁሉም የመንግስት ሠራተኞች ለዞኑ ለውጥና ውጤት አንዱ ከሌላው ልምድ በመቅሰም በትጋት እንዲሠሩ ዋና አስተዳዳሪው መልዕክት አስተላልፈው፤ የዕውቅና አሰጣጡ በተቻለ መጠን በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን ይደረጋል ብለዋል።
ዕውቅና የተሰጣቸው ፈፃሚዎችና የተቋም አመራሮች መመሪያን በተከተለ መልኩ ተግባራትን በቁርጠኝነት በመፈፀም ለውጤት መብቃታቸውን ገልፀው፤ በተሰጣቸው ዕውቅና ተደስተው በቀጣይም ይበልጥ ተግተው እንደሚሠሩ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በመርሐ ግብሩ የጡረታ ጊዜያቸው ደርሶ የሚወጡ አካላትም ዕውቅና ተሰጥቷቸው ተሸኝተዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ