የኣሪ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ የፐብሊክ ሰረቫንት ቀንን በማስመልከት በአፈፃፀማቸው የተሻሉ ተቋማትና ግለሰቦች ዕውቅና ተሰጣቸው
ሠራተኞችን መመዘን፣ ማበረታታትና መደገፍ ብሎም ማሰልጠን በሚሠሩባቸው ዘርፎች በተሻለ ሞራል ሥራቸውን እንዲከውኑ ያስችላል፤ ይህ ደግሞ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ጭምር ነው ያሉት የኣሪ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ አቶ አሸብር ጋልሶ ናቸው።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ እንደገለፁት፤ ፐብሊክ ሰርቫንት በሀገሪቱ ለውጥ ሂደት ውስጥ አይተኬ ሚና አላቸው።
በበቂ ሁኔታ ሠራተኞችና ሀብት በሌለበት በውስን ባለሙያዎች በጋራ ቅንጅት የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ በቁርጠኝነት የሠሩ አካላትን አበረታትው፤ በቀጣይም ጠንክረው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
ሁሉም የመንግስት ሠራተኞች ለዞኑ ለውጥና ውጤት አንዱ ከሌላው ልምድ በመቅሰም በትጋት እንዲሠሩ ዋና አስተዳዳሪው መልዕክት አስተላልፈው፤ የዕውቅና አሰጣጡ በተቻለ መጠን በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን ይደረጋል ብለዋል።
ዕውቅና የተሰጣቸው ፈፃሚዎችና የተቋም አመራሮች መመሪያን በተከተለ መልኩ ተግባራትን በቁርጠኝነት በመፈፀም ለውጤት መብቃታቸውን ገልፀው፤ በተሰጣቸው ዕውቅና ተደስተው በቀጣይም ይበልጥ ተግተው እንደሚሠሩ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በመርሐ ግብሩ የጡረታ ጊዜያቸው ደርሶ የሚወጡ አካላትም ዕውቅና ተሰጥቷቸው ተሸኝተዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ