የጉራጌ ዞን የጸጥታ ምክር የ2017 ዓ.ም የማጠቃለያ ጉባኤ እያካሄደ ነው።
ሀዋሳ፡ መስከረም 09/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጉራጌ ዞን የጸጥታ ምክር ቤት ”ሰላማችን በማጽናት ለልማታችን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እንተጋለን” በሚል መሪ ሀሳብ የ2017 ዓ.ም የማጠቃለያ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ የህያ ሱልጣን ባስተላለፉት መልዕክት፥ በዞኑ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስራዎችን በተሟላ ሁኔታ ለመተግበርና ለማስቀጠል ሰላም መሰረታዊ ግብኣት በመሆኑ ሰላምን መጠበቅ ያስፈልጋል።
ሰላም እና ጸጥታ ያለህዝብ ተሳትፎ ማረጋገጥ አይቻልም ያሉት አቶ የህያ በተለይም በከተሞች የህዝብ ተሳትፎን ለማረጋገጥ ጠንካራ የድጋፍና ክትትል ስራ መሰራቱን አመላክተዋል።
የዞኑ መሰረታዊ የጸጥታ ችግሮች በመለየትና እንዲፈቱ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመምራት አበረታች ውጤት መመዝገቡና በዞኑ አንጻራዊ ሰላም በማስፈን የልማት ተሞክሮ መቀመሪያ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
የጸጥታ ተቋማት ዋነኛ ተልዕኮ የሆነውን የዜጎች ሰላምና ደህንነት የማረጋገጥ እንዲሁም ሀገርና ህዝብን ከየትኛውም ጥቃት የመከላከል እና ግቦችን ለማሳካት የጸጥታ ምክር ቤቱ ያስቀመጣቸውን አቅጣጫዎች ተከትሎ መስራት እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል።
በመድረኩ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ የብልጽግና ፓርቲ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል፣ የዞኑ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ከዞን ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ መላኩ ንማኒ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ