በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር በጂንካ ከተማ የሚገኙ የክልል ጤና ቢሮ የሥራ እንቅስቃሴ፣ የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ኦክሲጂን ማዕከልና በክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የጂንካ ህብረተሰብ ላቦራቶሪ ማዕከል ግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል።
በክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ነብዩ ቤዛ የጉብኝቱን አላማ በማስመልከት በሰጡት መግለጫ የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ሚኒስቴር ዴኤታ ደረጄ ዱጎማ (ዶ/ር) በክልሉ በላፉት ጊዜያት በከፈተኛ ሁኔታ ተከስቶ የነበረውን የወባ በሽታ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወባ ክትባት ዘመቻ ያስጀምራሉ ብለዋል።
በጤና ተቋማት ለዜጎች የሚሰጠውን የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ለማቀላጠፍ ትኩረት የሚያደርግ ሲሆን ጉብኝቱ በየአካባቢው ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን ለማስቀጠልና ውስንነቶችን በማረም በኩል ከፈተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖር ተመልክቷል ።
ዘጋቢ፡ ጄታ ታገሠ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚወጡ ተመራቂ ሰልጣኞች በሰለጠኑበት ዘርፍ ሀገሪቱ ለጀመረችው የብልጽግና ጉዞ የድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ
ለትውልድ ግንባታ መሠረት ለሆነው የሞዴል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ትኩረት ተሰጥቶ ሊሠራ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ምሁር-አክሊል ወረዳ በመንግስትና በህብረተሰቡ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው