“በቤንች ሸኮ ዞን በጉራፈርዳ ወረዳ አሁን ላይ አንፃራዊ ሠላም በመገኘቱ የአካባቢው ማህበረሰብ ወደ ልማት መግባት ችሏል” ሲሉ የወረዳው ነዋሪዎች ተናገሩ
በዞኑ የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም ዘላቂ ለማድረግ በየደረጃው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የቤንች ሸኮ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ አስታውቋል።
አቶ ዳዊት አሰፋና አቶ ባዬ አወቀ በቤንች ሸኮ ዞን የጉራፈርዳ ወረዳ ነዋሪዎች ናቸው።
ነዋሪዎቹ በወረዳው ባለፉት አመታት ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ በአካባቢው ልማትና ዕድገት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሮ እንደነበር ተናግረዋል
አሁን ላይ በወረዳው አንፃራዊ ሠላም በመገኘቱ የአካባቢው ማህበረሰብ ወደ ልማት መግባት መቻሉን ነው የተናገሩት።
በወረዳው የተገኘውን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
የጉራፈርዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ስንታየሁ ከርካ ከዚህ ቀደም በወረዳው በነበረው የፀጥታ ችግር ለበርካቶች ሞት መፈናቀል የንብረት ውድመት ምክንያት ሆኖ እንደነበር ጠቁመዋል።
የወረዳውን ሰላምና ልማት ዳግም ለመመለስ አመራሩ በየደረጃው ከሚገኙ የፀጥታ አካላትና የሀይማኖት መሪዎች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ጋር በመቀናጀት ሰፊ ስራ መስራቱን ነው የተናገሩት፡፡
በአሁኑ ወቅት ወረዳው ወደ ቀደመ ሰላሙ በመመለሱ ያሉ አልሚ ባለሀብቶችን ጨምሮ ማህበረሰቡ ወደ ልማት ስራ እንዲገቡ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኮጁ ባዳካች በበኩላቸው በዞኑ ባለፉት አመታት በተለያዩ ወረዳዎች የተለያዩ አጀንዳዎችን መነሻ በማድረግ ፀረ ሠላም ሀይሎች የሠላም ዕጦት እንዲፈጠር ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
በዞኑ የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም ዘላቂ ለማድረግ በየደረጃው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ