የአገር አቀፍ የህጸናት ፓርላማ የ2015 ዓ.ም የክረምት ወራትና የመደበኛ እቅድ አፈጻጸምን ገመገመ
በዚሁ መድረክ የ2016 ዓ.ም የህጸናት ፓርላማ መነሻ እቅድ ዙሪያም ውይይት ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ህጸናት ፓርላማ ዋና አፈ ጉባኤ ህጻን ቅዱስ ሞላ በዚሁ ጊዜ እንዳለው ፓርላማው የህጻናትን መብትና ደህንነት በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ዙሪያ ዘርፉን ከሚደግፉ ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ይገኛል።
የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ዓለሚቱ ኡሙድ በበኩላቸው የህጸናት የመማር መብታቸው እንዲረጋገጥ፣ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ እንዲሁም ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸው እንዲጎለብት የሁሉም ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል።
የሁሉም ክልል የህጸናት ፓርላማ አፈ ጉባኤዎች የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም እና በሂደቱ የተገኙ ተሞክሮዎችንና ያጋጠሙ ችግሮችን ሪፖርት በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የፓርላማ አባለቱ በአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሞች በመሳተፍ ችግኞችን መትከል፣ ለተቸገሩ ህጸናት የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረግ እንዲሁም ሌሎች ሰብአዊ ድጋፎችን ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር ማድረግ መቻላቸውን በሪፖርታቸው አመላክተዋል።
“ተወደደሪና ንቁ ሕጻናት ለዘመናዊት ኢትዮጵያ”፣ “ለዛሬዎቹ ሕጻናት ፍቅርና በጎነት እናውርስ” በሚል መሪ ቃል የአፍሪካ ህጻናት ቀን በአፍሪካ ለ33ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ32ኛ ጊዜ በነገው ዕለት ይከበራል።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ