የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) መልዕክት፡-
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!
ጊዜን፣ ፀጋዎችን፣ የመልማት አቅሞችን፣ ሌሎችንም ዕድሎች ከወትሮው በተለየ መንገድ፣ በተስፋና በፅናት መንፈስ፣ በይቻላል የእመርታ መነፅር ማስተዋል፤ ለእመርታዊ ለዉጥ ብርቱ ዐቅም ይሆናል።
ለእመርታዊ ለዉጥ፣ እመርታዊ እይታ፣ እመርታዊ ሀሳብ ያሻል። የሀሳብ እመርታ፣ የጉዳዮች መመልከቻ መነፅር ከፍ እንዲል፣ የእይታ እጥፋት እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ለፈጠራና ፍጥነት ምክንያት ይሆናል፤ የትጋትና የዉጤት እመርታ እዉን እንዲሆንም ያስችላል።
የማይቻሉ የሚመስሉ ጉዳዮች እንደሚቻሉ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በእመርታዊ እይታና ትጋት ያሳካናቸዉ ጉዳዮች ምስክሮች ናቸዉ። እናም እያንዳንዱን ቀን፣ እያንዳንዱን ወር በአጠቃላይ ጊዜን፣ እዉቀትን፣ ጉልበትን፣ ፀጋዎችን፣ የሕዝብ ዐቅሞችን፣ የመልማት እምቅ ዕድሎችን…ወዘተ በእመርታ መነፅር መግራት፣ መምራት ለእመርታዊ ለዉጥ መሠረት ነዉ።

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ