የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) መልዕክት፡-
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!
ጊዜን፣ ፀጋዎችን፣ የመልማት አቅሞችን፣ ሌሎችንም ዕድሎች ከወትሮው በተለየ መንገድ፣ በተስፋና በፅናት መንፈስ፣ በይቻላል የእመርታ መነፅር ማስተዋል፤ ለእመርታዊ ለዉጥ ብርቱ ዐቅም ይሆናል።
ለእመርታዊ ለዉጥ፣ እመርታዊ እይታ፣ እመርታዊ ሀሳብ ያሻል። የሀሳብ እመርታ፣ የጉዳዮች መመልከቻ መነፅር ከፍ እንዲል፣ የእይታ እጥፋት እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ለፈጠራና ፍጥነት ምክንያት ይሆናል፤ የትጋትና የዉጤት እመርታ እዉን እንዲሆንም ያስችላል።
የማይቻሉ የሚመስሉ ጉዳዮች እንደሚቻሉ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በእመርታዊ እይታና ትጋት ያሳካናቸዉ ጉዳዮች ምስክሮች ናቸዉ። እናም እያንዳንዱን ቀን፣ እያንዳንዱን ወር በአጠቃላይ ጊዜን፣ እዉቀትን፣ ጉልበትን፣ ፀጋዎችን፣ የሕዝብ ዐቅሞችን፣ የመልማት እምቅ ዕድሎችን…ወዘተ በእመርታ መነፅር መግራት፣ መምራት ለእመርታዊ ለዉጥ መሠረት ነዉ።

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ