የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የእምርታ ቀንን በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት:-
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሀገር በቀል እሳቤዎች ሀገራዊ አቅሞችን መጠቀም ያስቻሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችንና በርካታ የልማት ኢኒሼቲቮችን በመተግበር እንዲሁም የተረጂነትና የጠባቂነት አስተሳሰብንና አመለካከትን በመስበር፤ አይቻልም በተባሉ መስኮች ጭምር ምርታማነትን በማሳደግ የታሪክ ዕጥፋት ማስመዝገብ ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለው ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ዕውን በማድረግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መሰረት የጣሉ አስደናቂ እምርታዎችን ማስመዝገብ ችለናል፡፡
በሁሉም የኢኮኖሚ እድገት ዘርፎች እና የዘላቂ ልማት ግቦች ማሳካት የቻልነው ተጨባጭ እምርታዊ ለውጥ፤ የጠራ ራዕይ በመሰነቅ፤ ተቋማዊ አቅሞችን በማጎልበትና በየወቅቱ የሚገጥሙንን ፈተናዎች ተባብረን በጽናት በመሻገር በእጃችን ያሉን ፀጋዎችና የመልማት አቅሞች በአግባቡ ተጠቅመን በህብረት ተግተን በመስራት ባጭር ጊዜ ውስጥ ብልጽግናችንን በተሟላ ሁኔታ በእጃችን ማረጋገጥ እንደምንችል ማሳያ ናቸው።
ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን በጋራ ጥረትና ትጋት እናረጋግጣለን!!
“እምርታ ለዘላቂ ልማት ከፍታ”

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ