የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል ሲከበር የእርሳቸውን አርዓያ በመከተል መልካም ተግባራትን በማከናወን ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፣ ነሐሴ 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቦንጋ ከተማ አስተዳደር የተንጎላ መስጂድ አስተዳዳሪ አሚር መሐመድ ከድር ለ1500ኛው የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ህዝበ-ሙስሊሙ የነብዩ መሐመድን የልደት በዓል ሲያከብር የእርሳቸውን ደግነት፣ ሰው አክባሪነትና መልካም አርአያነት በመከተል ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ነብዩ መሐመድ ለተራበ የሚመግቡ፣ የተቸገረን ሁሉ ጠያቂና የመልካም ስብዕና ባለቤት በመሆናቸው ፤ የእርሳቸውን በጎ ባህርይ መላበስ ይገባል በማለት አሳስበዋል።
የነብዩ መወለድ ህዝበ-ሙስሊሙ ብርሀን እንዲመለከት ያስቻለ በመሆኑ፤ ይህንን ብርሀን በመከተል ለአላህ ተገዢ መሆን እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
በሁሉም አካባቢዎች በዓሉ ሲከበር ለኢትዮጵያ ሠላም ዱአ በማድረግና ለተቸገሩ ወገኖች በመድረስ እንዲሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም እንኳን ለ1500ኛው የነብዩ መሐመድ የልደት ቀን በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ ማርታ ታምሩ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የጌዴኦን ተፈጥሮአዊና ባህላዊ መልክዓ-ምድር በመንከባከብ፣ አካባቢውን ለቱሪስት መስህብና ለኢኮኖሚ እድገት ለማዋል በትኩረት እየሰራ ነውሀዋሳ፡ መጋቢት 10/2018 (ደሬቴድ)የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የጌዴኦን ተፈጥሮአዊና ባህላዊ መልክዓ-ምድር በመንከባከብ፣ አካባቢውን ለቱሪስት መስህብና ለኢኮኖሚ እድገት ለማዋል በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጿል፡፡
“ጠንካራ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት የትምህርት ጥራትን ያስጠብቃል“ – ደስታ ገነሜ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ