የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል ሲከበር የእርሳቸውን አርዓያ በመከተል መልካም ተግባራትን በማከናወን ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፣ ነሐሴ 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቦንጋ ከተማ አስተዳደር የተንጎላ መስጂድ አስተዳዳሪ አሚር መሐመድ ከድር ለ1500ኛው የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ህዝበ-ሙስሊሙ የነብዩ መሐመድን የልደት በዓል ሲያከብር የእርሳቸውን ደግነት፣ ሰው አክባሪነትና መልካም አርአያነት በመከተል ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ነብዩ መሐመድ ለተራበ የሚመግቡ፣ የተቸገረን ሁሉ ጠያቂና የመልካም ስብዕና ባለቤት በመሆናቸው ፤ የእርሳቸውን በጎ ባህርይ መላበስ ይገባል በማለት አሳስበዋል።
የነብዩ መወለድ ህዝበ-ሙስሊሙ ብርሀን እንዲመለከት ያስቻለ በመሆኑ፤ ይህንን ብርሀን በመከተል ለአላህ ተገዢ መሆን እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
በሁሉም አካባቢዎች በዓሉ ሲከበር ለኢትዮጵያ ሠላም ዱአ በማድረግና ለተቸገሩ ወገኖች በመድረስ እንዲሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም እንኳን ለ1500ኛው የነብዩ መሐመድ የልደት ቀን በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ ማርታ ታምሩ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ