በምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የኮሌጁ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ካሳ እንዳሉት ኮሌጁ ባለፉት 14 ዓመታት በተለያዩ መስኮች በአጫጭር እና ቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በዲግሪ እና በማስተርስ ዲግሪ ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል።
ኮሌጁ ከመምር ማስተማር ጎን ለጎን የሸማ ፓርክን ጨምሮ 10 የቢዝነስ ድርጅቶችን በመክፈት ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉንም አቶ አለማየሁ ካሳ ገልጸዋል።
የዕለቱ ክብር እንግዳ እና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አዲሱ አዳሙ (ዶ/ር) እንዳሉት ትምህርት ለአንድ አገር የሚኖረው ፋይዳ የላቀ በመሆኑ የግልም ሆነ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለይም የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በትኩረት መሥራት ይጠበቅባቸዋል።
ተመራቂዎች የሥራ ፈጣሪ ሆነው ለአገሪቱ ዕድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ የመምሪያው ሀላፊ ጥሪ አቅርበዋል።
በኮሌጁ ቆይታቸው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂዎች መዳሊያና ዋንጫ ተሸልመዋል።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ