በምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የኮሌጁ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ካሳ እንዳሉት ኮሌጁ ባለፉት 14 ዓመታት በተለያዩ መስኮች በአጫጭር እና ቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በዲግሪ እና በማስተርስ ዲግሪ ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል።
ኮሌጁ ከመምር ማስተማር ጎን ለጎን የሸማ ፓርክን ጨምሮ 10 የቢዝነስ ድርጅቶችን በመክፈት ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉንም አቶ አለማየሁ ካሳ ገልጸዋል።
የዕለቱ ክብር እንግዳ እና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አዲሱ አዳሙ (ዶ/ር) እንዳሉት ትምህርት ለአንድ አገር የሚኖረው ፋይዳ የላቀ በመሆኑ የግልም ሆነ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለይም የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በትኩረት መሥራት ይጠበቅባቸዋል።
ተመራቂዎች የሥራ ፈጣሪ ሆነው ለአገሪቱ ዕድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ የመምሪያው ሀላፊ ጥሪ አቅርበዋል።
በኮሌጁ ቆይታቸው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂዎች መዳሊያና ዋንጫ ተሸልመዋል።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ