በምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የኮሌጁ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ካሳ እንዳሉት ኮሌጁ ባለፉት 14 ዓመታት በተለያዩ መስኮች በአጫጭር እና ቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በዲግሪ እና በማስተርስ ዲግሪ ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል።
ኮሌጁ ከመምር ማስተማር ጎን ለጎን የሸማ ፓርክን ጨምሮ 10 የቢዝነስ ድርጅቶችን በመክፈት ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉንም አቶ አለማየሁ ካሳ ገልጸዋል።
የዕለቱ ክብር እንግዳ እና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አዲሱ አዳሙ (ዶ/ር) እንዳሉት ትምህርት ለአንድ አገር የሚኖረው ፋይዳ የላቀ በመሆኑ የግልም ሆነ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለይም የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በትኩረት መሥራት ይጠበቅባቸዋል።
ተመራቂዎች የሥራ ፈጣሪ ሆነው ለአገሪቱ ዕድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ የመምሪያው ሀላፊ ጥሪ አቅርበዋል።
በኮሌጁ ቆይታቸው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂዎች መዳሊያና ዋንጫ ተሸልመዋል።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የተመራ ሉዑክ ለተለያዩ የልማት ሥራዎች ጉብኝት ኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ ገቡ
በባህር ዛፍ የተያዙ ለም መሬቶችን የምግብ ዋስትናን ሊያረጋግጡ በሚችሉ ሰብሎች መተካት መጀመሩ የሚበረታታ መሆኑ ተገለጸ
ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ