በምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የኮሌጁ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ካሳ እንዳሉት ኮሌጁ ባለፉት 14 ዓመታት በተለያዩ መስኮች በአጫጭር እና ቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በዲግሪ እና በማስተርስ ዲግሪ ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል።
ኮሌጁ ከመምር ማስተማር ጎን ለጎን የሸማ ፓርክን ጨምሮ 10 የቢዝነስ ድርጅቶችን በመክፈት ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉንም አቶ አለማየሁ ካሳ ገልጸዋል።
የዕለቱ ክብር እንግዳ እና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አዲሱ አዳሙ (ዶ/ር) እንዳሉት ትምህርት ለአንድ አገር የሚኖረው ፋይዳ የላቀ በመሆኑ የግልም ሆነ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለይም የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በትኩረት መሥራት ይጠበቅባቸዋል።
ተመራቂዎች የሥራ ፈጣሪ ሆነው ለአገሪቱ ዕድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ የመምሪያው ሀላፊ ጥሪ አቅርበዋል።
በኮሌጁ ቆይታቸው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂዎች መዳሊያና ዋንጫ ተሸልመዋል።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የጌዴኦን ተፈጥሮአዊና ባህላዊ መልክዓ-ምድር በመንከባከብ፣ አካባቢውን ለቱሪስት መስህብና ለኢኮኖሚ እድገት ለማዋል በትኩረት እየሰራ ነውሀዋሳ፡ መጋቢት 10/2018 (ደሬቴድ)የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የጌዴኦን ተፈጥሮአዊና ባህላዊ መልክዓ-ምድር በመንከባከብ፣ አካባቢውን ለቱሪስት መስህብና ለኢኮኖሚ እድገት ለማዋል በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጿል፡፡
“ጠንካራ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት የትምህርት ጥራትን ያስጠብቃል“ – ደስታ ገነሜ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ