በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ
የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘለቀ ደምሴ እንደገለፁት ከወቅቱ ቴክኖሎጂ ጋር የሚራመድ በዕቅድ የሚመራና የመፈፀም አቅሙን በየጊዜው የሚያሳድግ፣ የተገልጋይ እርካታን የሚፈጥር ባለሙያና ሲቪል ሰርቫንት ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ኃላፊው አክለውም ቆጥሮ የሚፈፅም ባለሙያ ከመፍጠር አንፃር ተግዳሮቶች እና ውስንነቶች በመኖራቸው የሰቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ከዕቅድ ጀምሮ ባሉ የለወጥ ሥራዎች ዙርያ በወረዳው ላሉ ሲቪል ሰርቫንት በሃና ከተማ ሰልጠና ሰጥቷል።
ከዕቅድ ጀምሮ በአገልጋይነት መንፈስ የሚሰራውን ሥራ በአግባቡ አውቆት መፈፀም እንድችል ስልጠናው ማሰፈለጉን አመላክተዋል።
የህዝብ ክንፍን ያሳተፈ የምዘና ሥርዓት ሊጠናከር እንደሚገባም ተመላክቷዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ