በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ
የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘለቀ ደምሴ እንደገለፁት ከወቅቱ ቴክኖሎጂ ጋር የሚራመድ በዕቅድ የሚመራና የመፈፀም አቅሙን በየጊዜው የሚያሳድግ፣ የተገልጋይ እርካታን የሚፈጥር ባለሙያና ሲቪል ሰርቫንት ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ኃላፊው አክለውም ቆጥሮ የሚፈፅም ባለሙያ ከመፍጠር አንፃር ተግዳሮቶች እና ውስንነቶች በመኖራቸው የሰቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ከዕቅድ ጀምሮ ባሉ የለወጥ ሥራዎች ዙርያ በወረዳው ላሉ ሲቪል ሰርቫንት በሃና ከተማ ሰልጠና ሰጥቷል።
ከዕቅድ ጀምሮ በአገልጋይነት መንፈስ የሚሰራውን ሥራ በአግባቡ አውቆት መፈፀም እንድችል ስልጠናው ማሰፈለጉን አመላክተዋል።
የህዝብ ክንፍን ያሳተፈ የምዘና ሥርዓት ሊጠናከር እንደሚገባም ተመላክቷዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
ታሪክ፣ ባህሎችና ቅርሶችን ጠብቆ ማሳደግ ለቱሪዝም ልማትና ለህዝቦች ትስስር ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተጠቆመ
በኣሪ ወረዳ ያለው የመንገድ ችግር በማህበራዊ ህይወታቸው ሆነ በኢኮኖሚያቸው ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መሆኑን የአከባቢው ነዋሪዎችና አሽከርካሪዎች ገለጹ
የእንሰት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከ69 ሺህ 1 መቶ በላይ ሄክታር ማሳ በእንሰት መሸፈን መቻሉን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የዳዉሮ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ