በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ
የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘለቀ ደምሴ እንደገለፁት ከወቅቱ ቴክኖሎጂ ጋር የሚራመድ በዕቅድ የሚመራና የመፈፀም አቅሙን በየጊዜው የሚያሳድግ፣ የተገልጋይ እርካታን የሚፈጥር ባለሙያና ሲቪል ሰርቫንት ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ኃላፊው አክለውም ቆጥሮ የሚፈፅም ባለሙያ ከመፍጠር አንፃር ተግዳሮቶች እና ውስንነቶች በመኖራቸው የሰቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ከዕቅድ ጀምሮ ባሉ የለወጥ ሥራዎች ዙርያ በወረዳው ላሉ ሲቪል ሰርቫንት በሃና ከተማ ሰልጠና ሰጥቷል።
ከዕቅድ ጀምሮ በአገልጋይነት መንፈስ የሚሰራውን ሥራ በአግባቡ አውቆት መፈፀም እንድችል ስልጠናው ማሰፈለጉን አመላክተዋል።
የህዝብ ክንፍን ያሳተፈ የምዘና ሥርዓት ሊጠናከር እንደሚገባም ተመላክቷዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የጌዴኦን ተፈጥሮአዊና ባህላዊ መልክዓ-ምድር በመንከባከብ፣ አካባቢውን ለቱሪስት መስህብና ለኢኮኖሚ እድገት ለማዋል በትኩረት እየሰራ ነውሀዋሳ፡ መጋቢት 10/2018 (ደሬቴድ)የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የጌዴኦን ተፈጥሮአዊና ባህላዊ መልክዓ-ምድር በመንከባከብ፣ አካባቢውን ለቱሪስት መስህብና ለኢኮኖሚ እድገት ለማዋል በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጿል፡፡
“ጠንካራ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት የትምህርት ጥራትን ያስጠብቃል“ – ደስታ ገነሜ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ