በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ
የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘለቀ ደምሴ እንደገለፁት ከወቅቱ ቴክኖሎጂ ጋር የሚራመድ በዕቅድ የሚመራና የመፈፀም አቅሙን በየጊዜው የሚያሳድግ፣ የተገልጋይ እርካታን የሚፈጥር ባለሙያና ሲቪል ሰርቫንት ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ኃላፊው አክለውም ቆጥሮ የሚፈፅም ባለሙያ ከመፍጠር አንፃር ተግዳሮቶች እና ውስንነቶች በመኖራቸው የሰቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ከዕቅድ ጀምሮ ባሉ የለወጥ ሥራዎች ዙርያ በወረዳው ላሉ ሲቪል ሰርቫንት በሃና ከተማ ሰልጠና ሰጥቷል።
ከዕቅድ ጀምሮ በአገልጋይነት መንፈስ የሚሰራውን ሥራ በአግባቡ አውቆት መፈፀም እንድችል ስልጠናው ማሰፈለጉን አመላክተዋል።
የህዝብ ክንፍን ያሳተፈ የምዘና ሥርዓት ሊጠናከር እንደሚገባም ተመላክቷዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የተመራ ሉዑክ ለተለያዩ የልማት ሥራዎች ጉብኝት ኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ ገቡ
በባህር ዛፍ የተያዙ ለም መሬቶችን የምግብ ዋስትናን ሊያረጋግጡ በሚችሉ ሰብሎች መተካት መጀመሩ የሚበረታታ መሆኑ ተገለጸ
ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ