በመኸር እርሻ ከ4ሺ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን አቅዶ እየሰራ መሆኑን የቁጫ አልፋ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለጸ
አርሶአደር መስፍን ማንደፎ በወረዳው ኮዶ ዎኖ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው፤ በ 2 ሄክታር ማሳ ላይ በማህበር ተደራጅተው ሰብል በማምረት ላይ እንደሚገኙ ገልጸው የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር በበቂ መጠን እና ጊዜ እንዲቀርብላቸው ጠይቀዋል።
ሌላኛው አርሶአደር ሳባ ሳና ዝናብን ጠብቀው የመኸር እርሻ ስራ ዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው መሬታቸውን በዘመናዊ የእርሻ ትራክተር በማረስ የበለጠ ተጠቃሚ ለመሆን ቢፈልጉም አቅርቦት ባለመኖሩ መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡
የቁጫ አልፋ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን በርገኔ እንዳብራሩት በ2017/18 መኸር በልዩ ትኩረት ከሚሰሩ የግብርና ተግባራት መካከል ጤፍ እና ቦለቄ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ ተናግረዋል ።
በአጠቃላይ 4ሺ 2 መቶ 46 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ የማሳ ሽፋኑ 89 ከመቶ ደርሷል ብለዋል።
ኃላፊው አክለውም በዘር ከተሸፈነው ማሳ 317 ሺህ 7 መቶ 80 ኩንታል ምርት ለማምረት ግብ መጣሉን አውስተው ከዚህ ውስጥ በዋና ዋና ሰብል በአጠቃላይ 2ሺህ 9 መቶ 62 ሄክታር ይለማል ብለዋል።
ዘጋቢ ፦ አሰግድ ተረፈ ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የጌዴኦን ተፈጥሮአዊና ባህላዊ መልክዓ-ምድር በመንከባከብ፣ አካባቢውን ለቱሪስት መስህብና ለኢኮኖሚ እድገት ለማዋል በትኩረት እየሰራ ነውሀዋሳ፡ መጋቢት 10/2018 (ደሬቴድ)የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የጌዴኦን ተፈጥሮአዊና ባህላዊ መልክዓ-ምድር በመንከባከብ፣ አካባቢውን ለቱሪስት መስህብና ለኢኮኖሚ እድገት ለማዋል በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጿል፡፡
“ጠንካራ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት የትምህርት ጥራትን ያስጠብቃል“ – ደስታ ገነሜ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በጋሞ ዞን የተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ