በመኸር እርሻ ከ4ሺ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን አቅዶ እየሰራ መሆኑን የቁጫ አልፋ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለጸ

በመኸር እርሻ ከ4ሺ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን አቅዶ እየሰራ መሆኑን የቁጫ አልፋ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለጸ

‎አርሶአደር መስፍን ማንደፎ በወረዳው ኮዶ ዎኖ ‎ቀበሌ ነዋሪ ናቸው፤ በ 2 ሄክታር ማሳ ላይ በማህበር ተደራጅተው ሰብል በማምረት ላይ እንደሚገኙ ገልጸው የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር በበቂ መጠን እና ጊዜ እንዲቀርብላቸው ጠይቀዋል።

‎ሌላኛው አርሶአደር ሳባ ሳና ዝናብን ጠብቀው የመኸር እርሻ ስራ ዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው መሬታቸውን በዘመናዊ የእርሻ ትራክተር በማረስ የበለጠ ተጠቃሚ ለመሆን ቢፈልጉም አቅርቦት ባለመኖሩ መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡

‎የቁጫ አልፋ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን በርገኔ እንዳብራሩት በ2017/18 መኸር በልዩ ትኩረት ከሚሰሩ የግብርና ተግባራት መካከል ጤፍ እና ቦለቄ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ ተናግረዋል ።

‎በአጠቃላይ 4ሺ 2 መቶ 46 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት  በዘር ለመሸፈን ታቅዶ  የማሳ ሽፋኑ 89 ከመቶ  ደርሷል ብለዋል።

‎ኃላፊው አክለውም በዘር ከተሸፈነው ማሳ 317 ሺህ 7 መቶ 80 ኩንታል ምርት ለማምረት ግብ መጣሉን አውስተው ከዚህ ውስጥ በዋና ዋና ሰብል በአጠቃላይ 2ሺህ 9 መቶ 62 ሄክታር ይለማል ብለዋል።

‎ዘጋቢ ፦ አሰግድ ተረፈ ከአርባምንጭ ጣቢያችን