በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ኮይቤ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 3 ልጆችን ተገላገለች
ከዚህ በፊት አራት ልጆችን በአራት ዙር የወለደች ሲሆን በአምስተኛው እርግዝና ሦስት ልጆችን መውለዷን ሆስፒታሉ አስታውቋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ የካሌንዶ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ አዳነች ገናሜ፤ በቅድመ ክትትል ሂደት ሦስት ልጆችን ማርገዟ ታወቆ ክትትል እየተደረገ መቆየቱን የኮይቤ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሀኪም አምባቸው አሰፋ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
አምባቸው አሰፋ (ዶ/ር) አክለውም በሆስፒታሉ ከሁለት በላይ መንትያ ሲወለድ የመጀመሪያ መሆኑን ገለጸው ከተወለዱ ሕፃናት ሁለቱ ወንዶች ሲሆኑ አንዷ ሴት መሆኗንና ሦስቱም ህጻናት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል።
በአንድ ጊዜ ሶስት ልጆችን በሰላም በመገላገሏ ደስተኛ መሆኗን የገለጸችው ወ/ሮ አዳነች ገናሜ፤ በሆስፒታሉ ከክትትል ጀምሮ እስከወሊድ ቀን ድረስ የጤና ባለሙያዎች ላደረጉት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርባለች።
ዘጋቢ: ጄታ ታገሠ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በስብዕና ግንባታ ስራ ላይ በማተኮር በስነ-ምግባር የታነፀ ዜጋን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአረጋዉያን ያስገነባዉን የመኖሪያ እና እንክብካቤ ማዕከል ስራ አስጀመረ
የትምህርት ዘርፍ መጠናከር ሀገሪቱ ወደ አዲስ የስልጣኔ ማማ ለመድረስ ለምታደርገው ጉዞ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ አስታወቀ