በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ኮይቤ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 3 ልጆችን ተገላገለች
ከዚህ በፊት አራት ልጆችን በአራት ዙር የወለደች ሲሆን በአምስተኛው እርግዝና ሦስት ልጆችን መውለዷን ሆስፒታሉ አስታውቋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ የካሌንዶ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ አዳነች ገናሜ፤ በቅድመ ክትትል ሂደት ሦስት ልጆችን ማርገዟ ታወቆ ክትትል እየተደረገ መቆየቱን የኮይቤ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሀኪም አምባቸው አሰፋ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
አምባቸው አሰፋ (ዶ/ር) አክለውም በሆስፒታሉ ከሁለት በላይ መንትያ ሲወለድ የመጀመሪያ መሆኑን ገለጸው ከተወለዱ ሕፃናት ሁለቱ ወንዶች ሲሆኑ አንዷ ሴት መሆኗንና ሦስቱም ህጻናት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል።
በአንድ ጊዜ ሶስት ልጆችን በሰላም በመገላገሏ ደስተኛ መሆኗን የገለጸችው ወ/ሮ አዳነች ገናሜ፤ በሆስፒታሉ ከክትትል ጀምሮ እስከወሊድ ቀን ድረስ የጤና ባለሙያዎች ላደረጉት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርባለች።
ዘጋቢ: ጄታ ታገሠ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በትምህርት ሴክተር እየገጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት የትምህርት አመራር ሪፎርም ማድረግ እንደሚያስፈልግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለጸ
በቀረበው የ6 ወራት የመስተዳድር ምክር ቤት እቅድ አፈፃፀም ላይ የምክር ቤቱ አባላት ላነሷቸዉ ጥያቄዎች ከሚመለከታቸው አካላት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጠ
የዲዚ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ የምስጋና በዓል “ከይ ቢያርግ” በምእራብ ኦሞ ዞን በቤሮ ወረዳ እየተከበረ ይገኛል