የ2018 የኢትዮጵያ የግብርና ናሙና ጥናት መረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የ2018 የኢትዮጵያ የግብርና ናሙና ጥናት መረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና በአርባ ምንጭ ከተማ እየተሰጠ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ስታስትስቲክስ ኤጀንሲ የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ስሜ አንበሴ እንዳሉት ከግብርና ጋር የተያያዙ ወጥነት ያላቸው አዳዲስ መረጃዎችን ለማሰባሰብ እና ለፖሊሲ አውጪዎች ግብአት ለማቅረብ ጥናቱ ያግዛል።
አክለውም የመረጃ ሠራተኞች ስልጠናውን በትጋት በመከታተል ትክክለኛ መረጃ በማሰባሰብ አገራዊ ሐላፊነታቸውን እንዲወጡ ሀላፊው መክረዋል።
የግብርና ነክ ናሙና ለጥናቱ በግብርናው ምርም ብሎም ለቀጣይ ፖሊሲ አውጪዎች ያለው ሚና የጎላ ነው ያሉት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ዲን ደግፈ አሰፋ (ዶ/ር) ናቸው።
በግብርና ናሙና ጥናት ስልጠና ላይ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 8 ዞኖች የተወጣጡ ከ290 በላይ ስልጣኞች በመሳተፍ ላይ ያሉ ሲሆን በእርሻ በቤት፣ እንስሳት፣ በንብ እና ሌሎች ግብርና ነክ መረጃዎች ላይ ያተኮረ ነው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ