ህፃናትን ከጉልበት ብዝበዛ ለማዳን በሚደረገው ጥረት ሁሉም የድርሻውን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ተጠየቀ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 06/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ህፃናትን ከጉልበት ብዝበዛ ለማዳን በሚደረገው ጥረት ሁሉም የድርሻውን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ተጠየቀ፡፡
ዓለም አቀፍ የህፃናት ጉልባት ብዝበዛ ማስወገድ ቀን በአዲስአበባ ራዲሰን ብሉ ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል።
በህጸናት ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን በድራማ መልክ ያሳየውንና ችግሩን በጋራ ለመፍታት በሚያግዙ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር የሚደረግበትን መድረክ ያዘጋጀው ደግሞ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ከኖርዌይ ሠራተኛ ማህበር ኮንፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ነው።
“ህጻናት” ማለት ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆነ ማንኛውም ሰው መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።
የህጻናት ጉልበት ብዝበዛ በባህሪው የልጆችን ልጅነት የሚነጥቅ ፣ ክብር የሚያሳጣ፣ አካላዊና ሥነ አዕምሯዊ እድገታቸውን የሚጎዳ እንዲሁም የትምህርት ዕድላቸውን የሚያጣብብ እና የሚዘጋ እንቅስቃሴ ነው።
ህጻናትን በባርነት ወይም ተመሳሳይ በሆነ ሁኔታ አስገድዶ ማሰራት ፤ ህጻናትን መሸጥና በህገ ወጥ መንገድ ማዘዋወር ፤ህጻናትን ለውትድርና በመመልመልና በመቅጠር ለግጭትና ለጦርነት ማሰራት እንዲሁም ህጻናትን ለወሲብና ወሲብ ቀስቃሽ በሆኑ ትዕይንቶች ማሰማራት አስከፊ ከሆኑ የህጸናት ጉልበት ብዝበዛዎች መካከል ተጠቃሾች ናቸው ተብሏል።
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚደንት አቶ አያሌው አህመድ እንደገለጹት በዓለማችን 160 ሚሊዮን ህፃናት፣ በአፍሪካ 72 ሚሊየን ህፃናት በኢትዮጵያ ደግሞ እድሜያቸው ከ5 እስከ 17 ውስጥ የሚገኙ 51 በመቶ የሚያህሉ ህጻናት ለጉልበት ብዝበዛ ተጋላጭ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
በጠቅላላ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ
የወሰድነውን የመራጭነት መታወቂያ ካርድ ተጠቅመን ድምፅ ለመስጠት እራሳችንን አዘጋጅተናል – የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች
የሚበጀንን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል – የማሻ ከተማ ነዋሪዎች