ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በከተማው አስተማማኝ ሰላም ማስፈኑ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 02/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በከተማው አስተማማኝ ሰላም ማስፈኑ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ከተማው የሚታወቅበትን የሰላም እሴት ለማስቀጠል ህዝቡን አጋዥ ሀይል አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ የገለፀው ደግሞ የከተማው ፖሊስ ነው፡፡
የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ከሆኑት መካከል አቶ ዳዊት ዳልጋ እና ሀምሳለቃ በቀለ ሀብቴ ሰላም ፀጥታ የጋራ ጉዳይ ነው ብለው ከተማው የሚታወቅበትን ሰላም ለማስቀጠል እየሰሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል ።
ሲስተር አስቴር ይዙ እና ወ/ሮ አበበች ባልቻም የከተማው ነዋሪዎች ሲሆኑ በከተማው የሚታየውን ሰላም ወደ አስተማማኝ ደረጃ እየደረሰ ይገኛል ብለዋል።
ኮማንደር ክበበው አዳል የአርባምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሲሆኑ ወንጀል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስን የሚያስከትል በመሆኑ በከተማውም ሰላምን ለማስፈን ሰፊ እና የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ይገኛል ።
በከተማዋ የተለያዩ ኩነቶች የሚከናወኑባት እና የቱሪስት መዳረሻ በመሆኗ ለሰላም እጦት መነሻ የሚሆኑ እንቅስቃሴዎች ሲከሰቱ ህብረተሰ በፍጥነት ለፀጥታ ሀይሉ እንደሚያሳውቅ አረጋግጠዋል።
ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ሀይማኖት ተቋማት፣ ከተለያዩ አደረጃጀቶች ፣ ከአከባቢው ነዋሪዎች እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን ሰፋፊ ስራዎችን በመስራት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪ ሰላም ወዳድ እና ሰሚ ማህበረሰብ ነው ያሉት ኮማንደር ክበበው፥ ይህንን በጎ እድል ለማስጠበቅ እንሰራለን ብለዋል።
ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በከተማው አስተማማኝ ሰላም እንዲፈጠር ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መቆየቱን ያወሱት የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገበዬሁ ፃራ፥ ህብረተሰቡ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመሆን የራሱን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ እየሰራ እንደሚገኝ አውስተው ሰላም እንዳይደፈርስ በ8 ቱ ቀበሌያት በየጊዜው ጠንካራ ውይይት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም የፀጥታ ስራን ህዝባዊ በማድረግ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ስልጠናዎች እየተሰጡ ይገኛሉ በዚህም ለውጥ እየተመዘገበ ነው ብለዋል።
ዘጋቢ ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በኮሬ ዞን የአስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች መልሶ የማደራጀት ምክክር መድረክ ተካሄደ
በአጋር ድርጅቶች የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች የመንግስት የልማት ክፍተት በመሙላት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያላቸው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
በሌማት ትሩፋት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን የምዕራብ አባያ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ