በነገው እለት እንደ ሀገር ለሚተከለው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም 1.6 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል መዘጋጀታቸውን የምእራብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መልኬ ኬላጌ ተናገሩ
በዞኑ ችግኞችን ወደተከላ ስፍራ ከማጓጓዝ ባለፈም 1.7 ሚሊየን ጉድጓዶች መዘጋጀታቸው ተጠቁሟል።
የምእራብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መልኬ ኬላጌ እንደተናገሩት በሰባት ወረዳ እና በሶስት የከተማ አስተዳደሮች በበልግ እና በመኸር ወራት 18 ሚሊየን የተለያዩ አይነት ችግኞች በበጀት አመቱ ተዘጋጅተው እስካሁንም 12 ሚሊየን ያህል ችግኞች ተተክለዋል።
በነገው እለት በአንድ ጀንበር ለሚከናወነው የተከላ ፕሮግራምም 1.6 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመው፤ ለዚሁ ተግባርም 1.7 ሚሊየን ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
1.2 ሚሊየን ሀገር በቀል የሆኑ የፍራፍሬ፣ የመኖ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን ቀሪዎቹ የውጪ ሀገር ዝርያ ያላቸው ችግኞች መሆናቸውንም አቶ መልኬ ጠቁመዋል።
ለተከላው በዞኑ 43 ሳይቶች መመረጣቸውን የጠቆሙት አቶ መልኬ፤ ከተመረጡት ሳይቶች ውስጥ አስሩ ቀጥታ ወደ ሲስተም የሚገቡ እና 42.6 ሄክታር የሚሸፍኑ እንደሆነ ተናግረዋል።
በተከላው ከአስሩ መዋቅር የተውጣጡ ከ150 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ አቶ መልኬ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አብዮት በቀለ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል