በነገው እለት እንደ ሀገር ለሚተከለው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም 1.6 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል መዘጋጀታቸውን የምእራብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መልኬ ኬላጌ ተናገሩ
በዞኑ ችግኞችን ወደተከላ ስፍራ ከማጓጓዝ ባለፈም 1.7 ሚሊየን ጉድጓዶች መዘጋጀታቸው ተጠቁሟል።
የምእራብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መልኬ ኬላጌ እንደተናገሩት በሰባት ወረዳ እና በሶስት የከተማ አስተዳደሮች በበልግ እና በመኸር ወራት 18 ሚሊየን የተለያዩ አይነት ችግኞች በበጀት አመቱ ተዘጋጅተው እስካሁንም 12 ሚሊየን ያህል ችግኞች ተተክለዋል።
በነገው እለት በአንድ ጀንበር ለሚከናወነው የተከላ ፕሮግራምም 1.6 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመው፤ ለዚሁ ተግባርም 1.7 ሚሊየን ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
1.2 ሚሊየን ሀገር በቀል የሆኑ የፍራፍሬ፣ የመኖ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን ቀሪዎቹ የውጪ ሀገር ዝርያ ያላቸው ችግኞች መሆናቸውንም አቶ መልኬ ጠቁመዋል።
ለተከላው በዞኑ 43 ሳይቶች መመረጣቸውን የጠቆሙት አቶ መልኬ፤ ከተመረጡት ሳይቶች ውስጥ አስሩ ቀጥታ ወደ ሲስተም የሚገቡ እና 42.6 ሄክታር የሚሸፍኑ እንደሆነ ተናግረዋል።
በተከላው ከአስሩ መዋቅር የተውጣጡ ከ150 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ አቶ መልኬ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አብዮት በቀለ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ23ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛና በማታ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 347 ተማሪዎችን አስመረቀ
በ2018 በጀት ዓመት የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል – አቶ ፍቅሬ አማን
ሚዲያን ለአዎንታዊ ነገር በመጠቀም ወጣቱ ሀገርን መገንባት አለበት – የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን