በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት 6ኛ ዙር 3ኛ የሥራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በኮላንጎ ከተማ እያካሄደ ነው
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኧሌ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ውድነሽ ሽቱ እንደገለፁት፤ ምክር ቤቱ በሕገ መንግስቱ በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሠረት የሕዝቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ሲሠራ መቆየቱን አስረድተዋል።
የምክር ቤቱ አባላት በ7ኛ መደበኛ ጉባኤ በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀትና በብቃት በመወያየት የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አፈ ጉባኤዋ አሳስበዋል።
ምክር ቤቱ ጉባኤውን ያለፈውን ቃለ ጉባኤ በማጽደቅ የጀመረ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት ዞኑ በኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በአቶ አርሻሎ አርካሌ እየቀረበ ይገኛል።
ጉባኤው ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚኖረው ቆይታው የዞኑ አስፈፃሚ መሥሪያ ቤቶችና የፍርድ ቤቱን የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርትና የ2018 ጠቋሚ ዕቅድ የሚገመግም እና ሌሎች የተለያዩ አጀንዳዎችና የዞኑን የ2018 ረቂቅ በጀትን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ