በአንድ ጀምበር ከ470 ሺህ በላይ ችግኞች ይተከላሉ – ጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም በአንድ ጀምበር ከ 470 ሺህ በላይ ችግኞች ለመትከል የሚያስችሉ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ።
በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም በአንድ ጀምበር ከ470 ሺህ በላይ የተለያዩ ለምግብነትና ሁሉ አቀፍ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገልጿል።
የይርጋጨፌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክፍሌ ጅክሶ ላለፉት ስድስት ዓመታት በመላው ሀገሪቱ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም በርካታ ለውጦችን እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል።
የአረንጓዴ አሻራ የደን ሽፋን ለማስፋትም ሆነ ለማስጠበቅ ፣ ዝናብን በወቅቱ ለማግኘት፣ ለተስተካከለ ስነምህዳር እና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ያለው አስተዋጽዖ ከፍተኛ እንደሆነም ገልጸዋል ።
በይርጋጨፌ ወረዳ የሀገር በቀል ዛፎችንና ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን በብዛት መትከል ላይ ትኩረት መደረጉንና ከነዚህም መካከል የደረሱ ፍራፍሬዎች እንዳሉ ነው የጠቆሙት ።
ዘንድሮም በአንድ ጀምበር ከ470 ሺህ በላይ የተለያዩ ዝሪያ ያላቸውን ችግኞችን በ490 ነጥብ 5 ካሬ መሬት ላይ ለመትከል መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፥ ለዚህም የሚሆኑ ሀገር በቀል ዛፎችን ጨምሮ የፍራፍሬ፣ የቡና፣ የእንሰትና ሌሎችም ችግኞች በበቂ ሁኔታ መዘጋጀታቸውንና በ18ቱም ቀበሌዎች ላይ ለመትከል አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።
ለሀገር አሻራችንን የምናሳርፍበት ቀን በመሆኑ ህብረተሰቡ በነቂስ ወጥቶ በችግኝ ተከላ ፕሮግራም ላይ መሳተፍ አለበት ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ።
ዘጋቢ፡ ለምለም ኦርሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የኣሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ ለ2018 በጀት ዓመት ከ2 ቢሊዮን 62 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ
ለሕዝቡ የሠላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት እንደሚገባ ተገለፀ
በነገው እለት እንደ ሀገር ለሚተከለው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም 1.6 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል መዘጋጀታቸውን የምእራብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መልኬ ኬላጌ ተናገሩ