ለሰብአዊ አገልግሎት ሥራ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ገለጸ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን የሰብአዊ አገልግሎት ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ አስታወቀ።
የሰው ልጆችን ችግር በማቃለል ተግባር ላይ የተመሠረተው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በተሠማራበት ሁሉ በሀገሪቱ የተለያዩ ሰብአዊ ተግባራትን በመፈጸም ላይ መሆኑ ተመላክቷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ማህበር በሰብአዊ አገልግሎት ተደራሽነት ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት በአርባ ምንጭ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
የጋሞ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ስለሺ ሲሳይ የማህበሩ ዓላማ ሰብአዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ በችግር ውስጥ ላሉ የሰው ልጆች አጋርነታችንን ማሳየት በመሆኑ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።
ቅርንጫ ጽ/ቤቱ በተለያዩ አከባቢዎች የሚከሰቱ የተፈጥሮ እና ሰው ሠራሽ ችግሮችን ለመቃለል የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የሥራ መሪዎች እየተሳተፉበት ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ