ለሰብአዊ አገልግሎት ሥራ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ገለጸ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን የሰብአዊ አገልግሎት ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ አስታወቀ።
የሰው ልጆችን ችግር በማቃለል ተግባር ላይ የተመሠረተው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በተሠማራበት ሁሉ በሀገሪቱ የተለያዩ ሰብአዊ ተግባራትን በመፈጸም ላይ መሆኑ ተመላክቷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ማህበር በሰብአዊ አገልግሎት ተደራሽነት ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት በአርባ ምንጭ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
የጋሞ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ስለሺ ሲሳይ የማህበሩ ዓላማ ሰብአዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ በችግር ውስጥ ላሉ የሰው ልጆች አጋርነታችንን ማሳየት በመሆኑ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።
ቅርንጫ ጽ/ቤቱ በተለያዩ አከባቢዎች የሚከሰቱ የተፈጥሮ እና ሰው ሠራሽ ችግሮችን ለመቃለል የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የሥራ መሪዎች እየተሳተፉበት ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ