ለሰብአዊ አገልግሎት ሥራ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ገለጸ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን የሰብአዊ አገልግሎት ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ አስታወቀ።
የሰው ልጆችን ችግር በማቃለል ተግባር ላይ የተመሠረተው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በተሠማራበት ሁሉ በሀገሪቱ የተለያዩ ሰብአዊ ተግባራትን በመፈጸም ላይ መሆኑ ተመላክቷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ማህበር በሰብአዊ አገልግሎት ተደራሽነት ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት በአርባ ምንጭ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
የጋሞ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ስለሺ ሲሳይ የማህበሩ ዓላማ ሰብአዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ በችግር ውስጥ ላሉ የሰው ልጆች አጋርነታችንን ማሳየት በመሆኑ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።
ቅርንጫ ጽ/ቤቱ በተለያዩ አከባቢዎች የሚከሰቱ የተፈጥሮ እና ሰው ሠራሽ ችግሮችን ለመቃለል የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የሥራ መሪዎች እየተሳተፉበት ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ23ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛና በማታ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 347 ተማሪዎችን አስመረቀ
በ2018 በጀት ዓመት የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል – አቶ ፍቅሬ አማን
ሚዲያን ለአዎንታዊ ነገር በመጠቀም ወጣቱ ሀገርን መገንባት አለበት – የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን