የአስፈጻሚ አካላት ካለባቸው ኃላፊነት መነሻ ለህዝቡ ኑሮ መሻሻል ተግተው ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 07/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአስፈጻሚ አካላት ካለባቸው ኃላፊነት መነሻ ለህዝቡ ኑሮ መሻሻል በተለይ ተግተው ሊሰሩ እንደሚገባቸው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አሳሰበ፡፡
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላት የግምገማ መድረክ በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ነዉ፡፡
የግምገማ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ፥ ምክር ቤቶች በዴሞክራሲ ስርዓት የህዝብ ተሳትፎ የሚገለፅባቸው ተቋማት መሆናቸውን ጠቁመው፥ ካላቸው ስልጣንና ኃላፊነት መነሻ የአስፈጻሚ አካላትን የስራ አፈጻጸም የሚገመገም መሆኑን አስረድተዋል።
እንደክልሉ ምክር ቤት ገለጻ፥ የክልሉ አስፈፃሚ አካላት በበጀት ዓመቱ ያላቸውን አፈጻጸም ለመገምገም ሲገናኙ ለሁለተኛ ዙር መሆኑን ያነሱት አቶ ወንድሙ፥ አስፈፃሚ አካላት ለህብረተሰቡ አገልገሎት ሊሠሯቸው ካቀዱት ዕቅድ አንጻር ይገመገማሉ ብለዋል።
አስፈጻሚ አካላት ለህዝቡ ኑሮ መሻሻል ሲባል በተለይ ተግተዉ ሊሰሩ እንደሚገባ አቶ ወንድሙ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች፥ የክልሉን የአስፈጻሚ አካላት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም በየዘርፉ መገምገማቸው የተመላከተ ሲሆን፥ የክልሉን አፈጻጸም በጠንካራና ደካማ ጎን የተለዩ ችግሮችን በቀጣይ ለማረም በሚስችል አኳኋን አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ወግደረስ አማረ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ