በ2017 የበልግ ምርት ዘመን በግብርና ምክረ ሐሳብና የተሟላ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው ስላረሱ የተሻለ ምርት እንደሚያገኙ በኣሪ ዞን የደቡብ ኣሪ ወረዳ አንዳንድ አርሶ አደሮች ተናገሩ
በምርት ዘመኑ ለክላስተር እርሻና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ ሲሰራ እንደነበር የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አስታውቋል።
እየናረ የመጣውን የገበያ ሁኔታ ለመቋቋም ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን የመጠቀም ባህላቸው ከጊዜ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የሚናገሩት የደቡብ ኣሪ ወረዳ አርሶ አደሮች፤ በመልማት ላይ ባለው የበልግ ምርት ዘመን የግብርና ምክረ ሐሳብንና የተሟላ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው ስላረሱ የተሻለ ምርት እንጠብቃለን ብለዋል።
የደቡብ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ደይዳቅ፤ በ2017 በልግ ምርት ዘመን በወረዳው 24 ሺህ ሔክታር መሬት በተለያዩ ምርቶች መሸፈኑን አመላክተው በምርት ዘመኑ ለኩታ ገጠም እርሻ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ እንደነበር አስረድተዋል።
በምርት ዘመኑ ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ ሲሰራ እንደነበር የሚናገሩት ኃላፊው፤ ከወትሮው ተመሣሣይ የምርት ዘመን የተሻለ ምርት እንደሚገኝም አረጋግጠዋል።
በቀጣይ አርሶ አደሩ በጊዜ የሚደርሱ ምርቶችን በወቅቱ በመሰብሰብና ለመኸር እርሻ ቅድመ ዝግጅት ላይ እንዲያተኩር መልዕክት ተላልፏል።
ዘጋቢ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በ2017 የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና የሚወስዱ የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወደ ተመደቡበት መፈተኛ ዩኒቨርሲቲ እየገቡ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለፀ
የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሣትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሴት አደረጃጀቶችን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
የሸኮ እና አካባቢዉ ምሁራን ጥናትና ምርምር ማህበር የ2017 በጀት አመት ማጠቃለያ ጉባኤዉን በሸካ ዞን በቴፒ ከተማ በማካሄድ ላይ ነው