በ2017 የበልግ ምርት ዘመን በግብርና ምክረ ሐሳብና የተሟላ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው ስላረሱ የተሻለ ምርት እንደሚያገኙ በኣሪ ዞን የደቡብ ኣሪ ወረዳ አንዳንድ አርሶ አደሮች ተናገሩ
በምርት ዘመኑ ለክላስተር እርሻና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ ሲሰራ እንደነበር የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አስታውቋል።
እየናረ የመጣውን የገበያ ሁኔታ ለመቋቋም ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን የመጠቀም ባህላቸው ከጊዜ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የሚናገሩት የደቡብ ኣሪ ወረዳ አርሶ አደሮች፤ በመልማት ላይ ባለው የበልግ ምርት ዘመን የግብርና ምክረ ሐሳብንና የተሟላ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው ስላረሱ የተሻለ ምርት እንጠብቃለን ብለዋል።
የደቡብ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ደይዳቅ፤ በ2017 በልግ ምርት ዘመን በወረዳው 24 ሺህ ሔክታር መሬት በተለያዩ ምርቶች መሸፈኑን አመላክተው በምርት ዘመኑ ለኩታ ገጠም እርሻ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ እንደነበር አስረድተዋል።
በምርት ዘመኑ ምርታማነትን የሚያሳድጉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ ሲሰራ እንደነበር የሚናገሩት ኃላፊው፤ ከወትሮው ተመሣሣይ የምርት ዘመን የተሻለ ምርት እንደሚገኝም አረጋግጠዋል።
በቀጣይ አርሶ አደሩ በጊዜ የሚደርሱ ምርቶችን በወቅቱ በመሰብሰብና ለመኸር እርሻ ቅድመ ዝግጅት ላይ እንዲያተኩር መልዕክት ተላልፏል።
ዘጋቢ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል