ብቁና ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት ለማፍራት የተሻሉትን ማበረታታት እንደሚገባ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞይ የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቫንትና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት በተሻለ አፈፃፀም ፊት ለወጡ ተቋማትና ግለሰቦች የዕውቅናና ሽልማት መርሃ-ግብር አካሂዷል።
በመርሀ ግብሩን ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታደለ ጥላሁን፥ በቡና ምርቷ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላት የይርጋጨፌ ከተማ የማደግ ሰፊ ዕድል ቢኖራትም ያሉ ዕድሎችን አዋህዶ ካለመጠቀም የተነሳ ዕድገቷ ሲጓተት መቆየቱን አስታውቀዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ያሉ ምቹ ዕድሎችን ወደ ድል ለመቀየር የሚያስችሉ ሀብት፣ ዕውቀትና ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የከተማዋን ዕድገት ለማፋጠን ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
እስከ አሁን ላስመዘገብናቸው ተስፋ ሰጪ ውጤቶች የከተማው ሲቪል ሰርቫንት ሚና ከፍተኛ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ታደለ፥ ሁሉንም መሸለም ባይቻል እንኳን በይበልጥ ወደ ፊት የወጡትን ለይቶ ዕውቅና መስጠት ለቀጣይ ተግባር የሞራል ስንቅ እንደሚሆን አብራርተዋል፡፡
የከተማው ሲቪል ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳዊት የጋ በበኩላቸው የሠራተኞችን የትምህርት መረጃ ከማጥራት አንስቶ በባህሪና ተግባር መዝኖ ተገቢውን ውጤት በመስጠት የፓብሊክ ሰርቫንቱን የመፈፀም አቅም ለማጎልበት በትኩረት እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
እስከ አሁን በተሠራው የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡት ዕውቅና የመስጠቱ ፣ የተያዙትን ዕቅዶች ለመፈፀም እየተጉ ያሉትን ማበረታታትና በዲጂታል የታገዙ አሠራሮችን በመዘርጋት ከተማዋን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ዕውቅናና ሽልማት የተበረከተላቸው አካላትም ባገኙት ክብር ሳይኩራሩ ለተሻለ ነገ እንደሚተጉ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ብቁና ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት ለማፍራት የተሻሉትን ማበረታታት እንደሚገባ ተገለፀ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል