15ኛው ዙር ኾራ ኣታ ኾንሶ በዓል አስመልክቶ በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 15ኛው ዙር ኾራ ኣታ ኾንሶ በዓልን አስመልክቶ በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው።
የኮንሶ ባህላዊ መልክዓ ምድር በዓለም ቅርስነት የተመዘገበበት 15ኛ ዓመትን በማስመልከት ነው ሲምፖዚየሙ እየተካሄደ ያለው።
የኮንሶ መልክዓ ምድር ሰኔ 20 ቀን 2003 ዓ.ም ለኢትዮጵያ 9 ነኛው የዓለም ቅርስ ሆኖ መመዝገቡ ይታወቃል።
በሲምፖዚየሙ የፌደራል የክልልና የዞኑ የስራ ኃላፊዎችና ምሁራን በተገኙበት ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ነው።
በነገው ዕለት በካራት ከተማ በአደባባይ በዐሉ በድምቀት ይከበራል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ