15ኛው ዙር ኾራ ኣታ ኾንሶ በዓል አስመልክቶ በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 15ኛው ዙር ኾራ ኣታ ኾንሶ በዓልን አስመልክቶ በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው።
የኮንሶ ባህላዊ መልክዓ ምድር በዓለም ቅርስነት የተመዘገበበት 15ኛ ዓመትን በማስመልከት ነው ሲምፖዚየሙ እየተካሄደ ያለው።
የኮንሶ መልክዓ ምድር ሰኔ 20 ቀን 2003 ዓ.ም ለኢትዮጵያ 9 ነኛው የዓለም ቅርስ ሆኖ መመዝገቡ ይታወቃል።
በሲምፖዚየሙ የፌደራል የክልልና የዞኑ የስራ ኃላፊዎችና ምሁራን በተገኙበት ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ነው።
በነገው ዕለት በካራት ከተማ በአደባባይ በዐሉ በድምቀት ይከበራል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ