15ኛው ዙር ኾራ ኣታ ኾንሶ በዓል አስመልክቶ በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 15ኛው ዙር ኾራ ኣታ ኾንሶ በዓልን አስመልክቶ በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው።
የኮንሶ ባህላዊ መልክዓ ምድር በዓለም ቅርስነት የተመዘገበበት 15ኛ ዓመትን በማስመልከት ነው ሲምፖዚየሙ እየተካሄደ ያለው።
የኮንሶ መልክዓ ምድር ሰኔ 20 ቀን 2003 ዓ.ም ለኢትዮጵያ 9 ነኛው የዓለም ቅርስ ሆኖ መመዝገቡ ይታወቃል።
በሲምፖዚየሙ የፌደራል የክልልና የዞኑ የስራ ኃላፊዎችና ምሁራን በተገኙበት ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ነው።
በነገው ዕለት በካራት ከተማ በአደባባይ በዐሉ በድምቀት ይከበራል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ