የአካባቢ ብክለትን በዘላቂነት በመከላከል የተሻለች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
“ፅዱ ኢትዮጵያን ባህል ማድረግ” በሚል መሪ ቃል ሁለተኛ ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ መድረክ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ መርሃግብሩ የጋራ ምክክር፣ የከተማ ፅዳትና የችግኝ ተከላም ተከናውኗል።
በንቅናቄው መድረክ ተገኝተው መልክት ያስተላለፉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ፤ ህብረተሰቡን በማስተባበር የሚሠሩ ሥራዎችን በማጠናከር የተሻለች ሀገርን ለትውልድ ለማውረስ መሥራት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ እንደገለፁት፤ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማንቃት ብክለትን ለመከላከል የቆሻሻ አያያዝ ሥርዓትና የአካባቢ እንክብካቤ ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል።
የአሪ ዞን ደንና አካባቢ ልማት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሣሁን ጠቃይ በበኩላቸው፤ ለ6 ወር በሚቆይ ፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ መድረክ “ፅዱ ኢትዮጵያን ባህል ማድረግ” በሚል መሪ ቃል የፕላስቲክ፣ የአፈር፣ የውሃና የድምፅ ብክለትን በመከላከል በቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ላይ የወጡ ሕጎችን ለማስፈፀም እንደሚተጉ ተናግረዋል።
ዘላቂ የከተማ ፅዳትና ውበት ሥራዎችን በማጠናከር ብክለቶችን ለመቆጣጠርና ለመከላከል በትኩረት ይሠራል ያሉት የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሲሳይ ጋልሺ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል